top of page

ኮሜርሻል ኖሚኒስ ፊቱን ወደ የውጪ ሀገር የሰው ሀይል አቅርቦትም ፊቱን ማዞሩን ተናገረ፡፡

  • 1 hour ago
  • 1 min read

ግንቦት 28/2018


በሶስተኛ ወገን አገልግሎት ዘርፍ የጥበቃ፣ የፅዳት፣ የሀብትና ንብረት አስተዳደር ስራ 60 ዓመት የሞላው ኮሜርሻል ኖሚኒስ አሁን ደግሞ ፊቱን ወደ የውጪ ሀገር የሰው ሀይል አቅርቦትም ፊቱን ማዞሩን ተናገረ፡፡


በ1958 ዓ.ም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተቋቋመው ድርጅቱ ለመንግስታዊም ሆኑ ለግል ተቋማት የፅዳትና የጥበቃ አገልግሎት የሚሆኑ የሰው ሀይል ከማቅረብ በተጨማሪ ፣ ህንፃና ንብረት አስተዳደር ፣ ከካሳ ክፍያ ጋር የተያያዙ የፈንድ አስተዳደርን ጨምሮ 13 ዓይነት አገልግሎቶችን እንደሚሰጥ ተናግሯል፡፡


በዚህም በመላ ሀገሪቱ በሚገኙት 32 ቅርንጫፎቹ ከ40 ሺህ በላይ ሰዎች የስራ እድል መፍጠሩን የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈጻሚ ኮማንደር ጥላሁን ፀጋዬ ነግረውናል፡፡


ድርጅቱ እስካሁን ሲሰጣቸው የነበሩ አገልግሎቶቹን ማዘመንና ማስፋት ላይ እንደሚበረታ እንዲሁም ወደ ውጪ ሀገር የሰለጠነ የሰው ሀይል ለማቅረብ እየሰራ እንደሆነ አስረድቷል፡፡


ለዚህም አንዲያግዝ በአጠቃላይ 127 ሚሊዮን ብር ወጪ የተደረገበት የስልጠና ማዕከል በገርጂ አካባቢ ተከፍቶ ስራ ጀምሯል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….



ፍቅሩ አምባቸው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page