top of page

‘’ከጎረቤት ሃገራት አንፃር ኢትዮጵያ ነዳጅ፣ የኤሌትሪክ ሀይል እና ውሃ፤ ለዜጎቿ በርካሸ የምታቀርብ ሀገር ናት’’ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ

  • sheger1021fm
  • 2 hours ago
  • 1 min read

ጥር 26/2018


ከጎረቤት ሃገራት አንፃር ኢትዮጵያ ነዳጅ ፣ የኤሌትሪክ ሀይል እና ውሃ ለዜጎቿ በርካሸ የምታቀርብ ሀገር መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ፡፡


የኤሌክትሪክ ሀይል ከኢትዮጵያ አንፃር 500 እጥፍ የሚያስከፍሉ ጎረቤት ሃገራት መኖራቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ንጹህ የመጠጥ ውሃም በርካሽ እያቀረበች መሆኗን ተናግረዋል፡፡

የነዳጅ ዋጋ በየወሩ ለምን ጭማሪ ይደረጋል? በሚል ከምክር ቤት አባላት ጥያቄ ተነስቶ ነበር፡፡


ለዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሰጡት ምላሽ እንደ አሜሪካ ባሉ ባደጉት ሃገራት የነዳጅ ዋጋ ልዩነቶች በየቀኑ በየማዲያው ይጠለፋል ብለዋል፡፡


ነዳጅ በኢትዮጵያ የሚሸጥበት ዋጋ አሁንም ከጎረቤት ሃገራት አንፃር ዝቅተኛ ነው ፤ ሲስተሙ ለዛ ስለማይመች አጭበርባሪዎችን ግን በልኩ ገና መቆጣጠር አልተቻለም ብለዋል፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page