‘’ከጎረቤት ሃገራት አንፃር ኢትዮጵያ ነዳጅ፣ የኤሌትሪክ ሀይል እና ውሃ፤ ለዜጎቿ በርካሸ የምታቀርብ ሀገር ናት’’ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ
- sheger1021fm
- 2 hours ago
- 1 min read
ጥር 26/2018
ከጎረቤት ሃገራት አንፃር ኢትዮጵያ ነዳጅ ፣ የኤሌትሪክ ሀይል እና ውሃ ለዜጎቿ በርካሸ የምታቀርብ ሀገር መሆኗን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ፡፡
የኤሌክትሪክ ሀይል ከኢትዮጵያ አንፃር 500 እጥፍ የሚያስከፍሉ ጎረቤት ሃገራት መኖራቸውን የጠቀሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ንጹህ የመጠጥ ውሃም በርካሽ እያቀረበች መሆኗን ተናግረዋል፡፡

የነዳጅ ዋጋ በየወሩ ለምን ጭማሪ ይደረጋል? በሚል ከምክር ቤት አባላት ጥያቄ ተነስቶ ነበር፡፡
ለዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በሰጡት ምላሽ እንደ አሜሪካ ባሉ ባደጉት ሃገራት የነዳጅ ዋጋ ልዩነቶች በየቀኑ በየማዲያው ይጠለፋል ብለዋል፡፡
ነዳጅ በኢትዮጵያ የሚሸጥበት ዋጋ አሁንም ከጎረቤት ሃገራት አንፃር ዝቅተኛ ነው ፤ ሲስተሙ ለዛ ስለማይመች አጭበርባሪዎችን ግን በልኩ ገና መቆጣጠር አልተቻለም ብለዋል፡፡
ትዕግስት ዘሪሁን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7












Comments