ከኢትዮጵያ በዘረፋ፣ በስጦታ በመሳሰሉት መንገዶች ከሀገር የወጡ ቅርሶችን በተለያየ ጊዜ እየተመለሱ ነው፡፡
- sheger1021fm
- Nov 25
- 1 min read
ህዳር 16 2018
ከኢትዮጵያ በዘረፋ፣ በስጦታ በመሳሰሉት መንገዶች ከሀገር የወጡ ቅርሶችን በተለያየ ጊዜ እየተመለሱ ነው፡፡
አሁንም ማስመለሱ ቀጥሏል፡፡
የቅርሶቹ መመለስ በተለይ ለጥናትና ምርምር እንደሚያግዝ ይነገራል፡፡
እነዚህ አዳዲስ የሚመጡ ቅርሶች ደግሞ የራሳቸውን ታሪክ ይዘው እንደመምጣታቸው ለጥናትና ምርምር አበርክቷቸው ከፍተኛ ነው ሲሉ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ዳይሬክተር ዶ/ር ዮሃንስ አድገ ተናግረዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲው የኢትዮጵያ ጥናትና ምርምር ተቋም ከ17 ሺ በላይ የሚሆኑ ቅርሶች በሙዚየሙ እንደሚገኙና እነዚህ ቅርሶች ከ40 በላይ የሚሆኑ የብሄር ብሄረሰቦችን ባህል ታሪክ ቋንቋ የሚገልጹ እንደሆኑ ነግሮናል፡፡
አሁንም ከተለያዩ የዓለም ሀገራት የኢትዮጵያን ቅርሶች ለማስመለስ የዝግጅት ስራ መጀመሩን አስረድተዋል ፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….
ማርታ በቀለ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s











Comments