top of page

የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ የእዳና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽንን ከገንዘብ ሚ/ር ጋር በመሆን ግምገማ ለማካሄድ በጠራው ስብሰባ ላይ የተቋሙ የስራ ሃላፊዎች ሳይገኙ ቀሩ፡፡

  • sheger1021fm
  • 8 hours ago
  • 1 min read

ታህሳስ 6/2018


የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፤ የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽንን ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በመሆን የፊት ለፊት ግምገማ ለማካሄድ በጠራው ስብሰባ ላይ የተቋሙ የስራ ሃላፊዎች ሳይገኙ ቀሩ፡፡


የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ እዳ እና ሃብት አስተዳደር ኮርፖሬሽንን ከገንዘብ ሚኒስቴር ጋር በመሆን የፊት ለፊት ግምገማ ላማካሄድ ለዛሬ ታህሳስ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ለ2:30 ቀጠሮ ይዞ የነበር ቢሆንም፤ የተቋሙን የስራ ሃላፊዎች የመገኘት ግዴታ ቢኖርባቸውም ሳይገኙ ቀርተዋል።


የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ መለስ መና የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ የቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የቦርድ አባላት በተገኙበት የተቋም አደረጃጀት፣ አሰራር ላይ ግልጽነት የሚፈልጉ ጉዳዮች ላይ ፊት ለፊት አስፈላጊ መሆኑ በቋሚ ኮሚቴው በኩል መልእክት እንዲደርስ እና በዚያ ላይ ወይይት ለማካሄድ ቀጠሮ መያዙን አስረድተዋል፡፡


ይሁንና የተቋሙ የስራ ሃላፊዎች እና የቦርድ ተወካዮች በስራ ምክንያት መገኘት እንዳልቻሉ አረጋግጠናል ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ree

የተቋሙ ሃላፊ እና የቦርዱ ሰብሳቢ በሌሉበት ወይይቱን ማካሄድ ካሰብነው ግብ አንጻር የተሳካ ይሆናል የሚል ግምት ስለሌለን ወይይቱ ወደ ሌላ ቀን ተዘዋውሯል ብለዋል።


የመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የስራ ሃላፊዎችን አስከ 3:20 ድርስ ጠብቆ ውይይቱን በቀጣይ ሁሉም አካላት በተገኙበት ይካሄዳል ሲል አስረድቷል፡፡


በመድረኩ ላይ የተገኙት ምክትል ስራ አስፈጻሚው በበኩላቸው ተቋሙ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ እንደሆነው አስረድተው የተቋሙን ቁመና ለማስተካካል በሌላ ቀን ዋና የስራ ሃላፊዎችም ሆነ ተቆጣጣሪው መስሪያ ቤት በተገኙበት ማካሄድ ይሻላል ካሉ በኋላ ስብሰባው ወደ ሌላ ቀን ተዘዋውሯል፡፡


ያሬድ እንዳሻው

Recent Posts

See All
በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡

ታህሳስ 6 2018 በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ የአካባቢው ቡሣ ጎኖፋ ወይም የእርዳታ ማስተባበሪያ በበኩሉ ድጋፍ እንዲቀጥል ለሚመለከተው የበላይ አካል ባሳውቅም ድጋፍ ግን ሊቀጥል አልቻለም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page