ከመንግስት መ/ቤቶች የጠፉ እና የባለቤትነት መታወቂያ ደብተራቸው በሌሎች ድርጅቶች ተመዝግቦ የተገኙ ተሽከርካሪዎች መኖራቸው በኦዲት ተረጋገጠ፡፡
- 7 hours ago
- 1 min read
ሰኔ 12/2018
ከመንግስት መ/ቤቶች የጠፉ እና የባለቤትነት መታወቂያ ደብተራቸው በሌሎች ድርጅቶች ተመዝግቦ የተገኙ ተሽከርካሪዎች መኖራቸው በኦዲት ተረጋገጠ፡፡
የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የመስሪያ ቤቶችን የተሽከርካሪ አያያዝና ስምሪትን በተመለከተ ባካሄደው ምርመራ በተለያዩ መ/ቤቶች ዘጠኝ መኪኖች ከናካቴው ጠፍተዋል ብሏል፡፡
ተጨማሪ ስድስት ሞተር ብስክሌቶችም የጠፋባቸው መ/ቤቶችን አግኝቻለሁ ብሏል፡፡
የተቋማቱን ስም ግን በኦዲት ሪፖርቱ አልተጠቀሰም፡፡

በሌላ በኩል የባለቤትነት መታወቂያ ደብተራቸው በሌሎች መ/ቤቶችና ድርጅቶች ስም ተመዝግቦ የተገኘ 595 የመንግስት ተሽከርካሪዎች በኦዲት ምርመራው ተገኝተዋል፡፡
እንዲሁም የሰሌዳ ቁጥር የሌላቸው 13 መኪኖች፣ 10 የሞተር ብስክሌቶችና 20 ትራክተሮች የንብረት አያያዛቸው በተፈተሹባቸው የመንግስት ተቋማት መገኘታቸውን የፌዴራል ዋና ኦዲተር መ/ቤት በሪፖርቱ ተናግሯል፡፡
ሌሎች 146 መኪኖች ፣ 27 ሞተር ብስክሌቶች፣ 18 የቁፋሮ መኪኖች ፣ 1 ሎደርና 1 ትራንክተር የሊብሬ ወይም የባለቤትነት መታወቂያ ደብተር ሊቀርብላቸው አልቻለም ተብሏል፡፡
ትዕግስት ዘሪሁን
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i





Comments