top of page

ኢትዮጵያዊያን ወደ ተለያዩ የአረብ ሀገራት ለስራ ከሄዱ በኋላ ለሚያጋጥሟቸው የጤና እክሎች ተከታትሎ መፍትሄ የሚሰጥ አሰራር የለም ተባለ፡፡

  • sheger1021fm
  • 5 minutes ago
  • 1 min read

ህዳር 15 2018

 

ኢትዮጵያዊያን ወደ ተለያዩ የአረብ ሀገራት ለስራ ከሄዱ በኋላ ለሚያጋጥሟቸው የጤና እክሎች ተከታትሎ መፍትሄ የሚሰጥ አሰራር የለም ተባለ፡፡

 

ይንን ችግርም ለመፍታ ይረዳል የተባለ እና የሀገር ውስጥ እና የአለም አቀፍ ተቋማት በጋራ የሚሰሩበት ፕሮጀክት ይፋ መደረጉን ሰምተናል።

 

ፕሮጀክቱን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ የስራ እና ክህሎት ሚኒስቴር፣ ቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል ሚሊኒየም ህክምና ኮሌጅ እና ሌሎችም መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ይሳተፉበታል ተብሏል።

 

ከዚህ ቀደም ሴቶች ለቤት ሰራተኝነት ወደ አረብ ሀገራት ሲሄዱ አንዴ ብቻ ተመርምረው እንደሚሄዱ እና በስራ ወቅት የጤና ችግር ቢገጥማቸው እንኳን ቋሚ ክትትል የሚያደርግ አሰራር እንዳልነበረ ሲነገር ሰምተናል፡፡

 

በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያውያኑ ለተለያ የጤና ቀውሶች ማለትም የአእምሮ ጤና መቃወክን ጨምሮ ሌሎች ችግሮችን እንደሚያተናግዱ ተመልክተናል ሲሉ የፕሮጀክቱ ዋና አስተባባሪ ዶክተር ካሳሁን ሀብታሙ ተናግረዋል፡፡

 

ይህንን እና ሌሎች ችግሮችን ይፈታል የተባለም ኢኖቬት የተሰኘ ፕሮጀክት ይፋ ተደርጓል፡፡

 

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇

 

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page