top of page

ኢትዮጵያ የአርብቶ አደሮችን ድንበር ተሻጋሪ ችግሮች ለመፍታት ከአካባቢው ሀገራት ጋር ተባብራ እንደምትሰራ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ኢፋ ሙለታ(ዶ/ር) ተናገሩ።

  • sheger1021fm
  • 2 minutes ago
  • 1 min read

ህዳር 13 2018

 

ኢትዮጵያ የአርብቶ አደሮችን ድንበር ተሻጋሪ ችግሮች ለመፍታት ከአካባቢው ሀገራት ጋር ተባብራ እንደምትሰራ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ኢፋ ሙለታ(ዶ/ር) ተናገሩ።

 

በአካባቢው ሀገራት የሚገኙ አርብቶ አደሮች ወቅቶችን በመከተል ከቤት እንስሳቶቻቸው ጋር ድንበር ተሻጋሪ እንቅስቃሴ እንደሚያደርጉ ሚኒስትር ዴኤታው አስታውሰዋል።

 

በዚህ እንቅስቃሴያቸውም ከግጦሽ መሬት እና ውሃ ጋር የተገናኙ ችግሮች ይገጥሟቸዋል ብለዋል።

 

እነዚህን ችግሮች ለመፍታት ኢትዮጵያ ከአካባቢው ሀገራት ጋር ተቀራርባ እንደምትሰራ ተናግረዋል።

 

የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነ መንግስታት ድርጅት (IGAD) ትኩረቱን በአካባቢው ሀገራት በሚገኙ አርብቶ አደሮች ላይ ያደረገ ውይይት እዚህ በአዲስ አበባ አካሂዷል።

 

ree

በውይይቱም በአካባቢው አርብቶ አደሮች መካከል ኢኮኖሚያዊ ትብብርን በማሳደግ ሠላማዊ ግንኙነትን ማጠናከር ማሳደግ እንደሚገባ ተጠቅሷል።

 

ኢጋድ ጁቡቲ ፤ ኤርትራ ፤ኢትዮጵያ ፤ ኬንያ ፤ ሶማሊያ ፤ ደቡብ ሡዳን፤ ዩጋንዳ እና ሡዳን ያሉበት ስብስብ እንደሆነ ይታወቃል።

 

በአፍሪካ አህጉር ካሉ 250 ሚሊየን አርብቶ አደሮች ከፍተኛውን ቁጥር የያዙት በእነዚሁ ሀገራት የሚገኙ እንደሆኑ ተጠቅሷል።

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇

 

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page