ኢትዮጵያ በአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጠና ተወዳደሪ ለመሆን የጉምሩክ አሰራሯን ቀልጣፋ ማድረግ እንደሚጠበቅባት ጥናት አመላከተ፡፡
- sheger1021fm
- Nov 25
- 1 min read
ህዳር 16 2018
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጠና ተወዳደሪ ለመሆን የጉምሩክ አሰራሯን ቀላል እና ቀልጣፋ ማድረግ እንደሚጠበቅባት ጥናት አመላከተ፡፡
ጥናቱን ያስጠናው የውጭ ጉዳይ ኢንስቲትዩት ሲሆን፤ ጥናቱን ለማጠናቀቅ 4 ወራት ፈጅቷል ተብሏል፡፡
የአፍሪካ ነፃ ንግድ ቀጠና 1.4 ቢሊዮን ሰዎችን እና ወደ 3 ትሪሊዮን ዶላር ዓመታዊ ጥቅል ምርት የሚይዝ መሆኑ በጥናቱ ተካቷል፡፡
በጥናቱ መሰረት የኢትዮጵያ የጉምሩክ አሰራር ውስብሰብ እና ቅልጣፍና የሚጎለው ነው፡፡ ይህም አገሪቱ ተወዳዳሪ እንዳትሆን የሚደርግ ነው ፡፡
ኢትዮጵያ ከ6 ዓመታት በፊት ባፀደቀቸው በዚህ ነፃ የንግድ ስምምነት ተጠቃሚ እና ተወዳዳሪ ለመሆን የህግ ማዕቀፎቿን ፣ የተቋማት ቅንጅት፤ የጉምሩክ ህጎቿን እና የመሰረተ ልማት ክፍተቷን ማስተካካል ይጠበቅባታል ተብሏል፡፡

ሀገሪቱ የንግድ ቀጠናውን የተመለከተ ፖሊሲ ቢኖራትንም በትግበራው እና ወደ ስራው መግባት ላይ ውስንነት መኖሩ ተጠቁሟል፡፡
የአገልግሎት እና ምርት ንግድ በዋናነት የሚያተኩረው አካባቢው ንግድ ላይ እንደሆነ የሚጠቁመው ጥናቱ አሁን በስራ ላይ ያለው ፖሊሲም አህጉር አቀፍ ንግድ ውድድር ላይ ከማተኮር ይልቅ ስራ እድል ፈጠራ፣ ከአባቢያዊ ንግድ ላይ ነው የሚተኩረው ይላል ጥናቱ፡፡
የኢንቨስትመንት የህግ ማዕቀፎችም ቢሆኑ ዋነኛ ትኩረታቸው በሀገር ውስጥ ላይ ነው ተብሏል፡፡
የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ሆኑ ሌሎች ተቋማት አሰራራቸውን በዲጂታል እና በአንድ መስኮት ማድረግ ፣ የተንዛዛ እና የማያሰራ የአሰራር ሥርዓቶቻቸቸውን ማስቀረት እንዳለባቸው ጥናቱ ይመክራል፡፡
ያሬድ እንዳሻው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s











Comments