አዋሽ ኢንሹራንስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጓዦችን የጉዞ የጤና ኢንሹራንስ ሽፋን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ስምምነት አደረገ።
- 3 hours ago
- 1 min read
የካቲት 12/2018
አዋሽ ኢንሹራንስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጓዦችን የጉዞ የጤና ኢንሹራንስ ሽፋን አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ስምምነት አደረገ።
ስምምነቱን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቺፍ ኮሜርሺያል ኦፊሰር አቶ ለማ ያዴቻ እና የአዋሽ ኢንሹራንስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ጅባት አለምነህ በዛሬው እለት ተፈራርመውታል።
በስምምነቱ መሰረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጓዦች የእጅ ስልካቸውን በመጠቀም ከኢትዮጵያ አየር መንገድ የሞባይል መተግበርያ ላይ የጉዞ ኢንሹራንስ ሽፋን አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላቸዋል ተብሏል።
የመድን አገልግሎቱ ተጓዦች ለተለያዩ ጉዳዮች ወደተለያዩ የዓለም ክፍሎች ሲጓዙ ለሚያገጥማቸው የተለያዩ የጤና እክሎች እንደሚውል ተጠቅሷል።
የዋሽ ኢንሹራንስ ዋና ስራ አሰፈፃሚ አቶ ጅባት አለምነህ "ከኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ ከአለም አቀፍ የጠለፋ ኢንሹራንስ ዋስትና ሰጪ ተቋማት እና ትራቭል አሲስታንት ጋር በመሆን በጉዞ ወቅት የሚያጋጥሙ አደጋዎችን ጉዳት የሚያካክስና የሚያቃልል አስተማማኝ የኢንሹራንስ ሽፋን አገልግሎትን በማቅረባችን ከፍተኛ የሆነ ደስታ ይሰማናል"ብለዋል።
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቺፍ ኮሜርሺያል ኦፊሰር አቶ ለማ ያዴቻ በበኩላቸው "ምንም እንኳን ስምምነቱ የተደረሰው አዋሽ ኢንሹራንስ በጨረታ ተወዳድሮ አሸንፎ ቢሆንም ኩባንያው ከቢሮክራሲ የነፃ በቢዝነስ መርህ የሚሰራ ተቋም በመሆኑ አብረን በመስራታችን ደስተኞች ነን " ብለዋል።
አዋሽ ኢንሹራንስ ሰየተፈረመ ካፒታሉ 4 ቢሊዮን ብር፣ የተከፈለ ካፒታሉ ከ3.5 ቢሊዮን ብር፣ የኩባንያው አጠቃላይ ኃብት ደግሞ ከ 13 ቢሊዮን ብር በላይ ደርሷል ተብሏል፡፡
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7












Comments