top of page

ነሀሴ 27 2017 - ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ለ 125,000 ወጣቶች የዲጂታል ስልጠና እድል ማመቻቸቱን ተናገረ፡፡

  • sheger1021fm
  • Sep 2
  • 1 min read

ዲጂታል ስልጠናው ቴክስታርት (Techstart) የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን ዛሬ ይፋ የተደረገ ነው፡፡


ስልጠናው በኢንተርኔት አማካይነት በኦንላይን የሚሰጥ ሲሆን በመጭዎቹ 3 ዓመታት ውስጥ የሚጠናቀቅ መሆኑን በላከልን መግለጫ ተናግሯል፡፡


እንድሜያቸው ከ18 ዓመት በላይ የሆናቸው ወጣቶችን በአማዞን ድረ ገፅ የክህሎት ማዕከል መሰረታዊ የክላወድ ስልጠና እንዲያገኙ ቀጣይነት ያለው የድረ ገፅ አገልግሎት የዲጂታል ስልጠናም አመቻችቻለሁ ብሏል፡፡


ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ይህን የማደርገው ተሰጥኦ ያላቸውን ወጣቶች በመደገፍ ቴክኖሎጂ መር የኢኮኖሚ ግቦችን እውን እንዲሆኑ ማህበራዊ ሀላፊነቴን ለመወጣት ነው ብሏል፡፡

ree

በቅርቡ የተመሰረተው ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ፋውንዴሸን ስልጠናውን በከፍተኛ ውጤት አጠናቅቀው አለም አቀፍ ተቀባይነት ያላቸው የምስክር ወረቀቶችን መውሰድ ለሚፈልጉ ሰልጣኞችም የመፈተኛ ክፍያዎች እንዲከፍሉላቸው ያመቻቻል ተብሏል፡፡


የፕሮግራሙን ይፋ መሆን አስመልክቶ የኩባንያው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚ ዊምቫን ሄሌፑት አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ስልጠና ወደ ኢትዮጵያ ያመጣነው የቴክኖሎጂ ኮከቦችን ለማፍራትም በማለም ነው ብለዋል፡፡


የዲጂታል ስልጠና ምዝገባው በቅርቡ ይጀመራል የተባለ ሲሆን ለስልጠናው ብቁ የሚያደርጉ መስፈርቶች በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ማህበራዊ ትስስር ገጾች ይፋ ይደረጋል ተብሏል፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
ጥቅምት 20 2018 - የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ

የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳቦች ያለ በቂ ምክንያት የማይፈፅሙ ተቋማት በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ቢሞክርም ባለው የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡ ተቋሙ የአስተዳደር በደል ደረሰብን እምባችን ይታበስልን የሚሉ አቤት ባዮችን ቅሬታ በመቀበል

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page