ነሀሴ 20 2017 - ኢትዮ ቴሌኮም ወደ የአፍሪካ ሀገሮች ገበያ ውስጥ ለመግባት እቅዴንና ቅድመ ዝግጅቶቼን አጠናቅቄአለሁ አለ
- sheger1021fm
- Aug 26
- 1 min read
ኢትዮ ቴሌኮም ከኢትዮዽያ ገበያ ወጥቼ ወደ ሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች ገበያ ውስጥ ለመግባት እቅዴንና ቅድመ ዝግጅቶቼን አጠናቅቄአለሁ አለ።
ኩባንያው በሀገር ውስጥ የዲጅታል አገልግሎት ከመስጠት አልፌ ከኢትዮጵያ ተሻግሬ በ #አፍሪካና ሌሎች ሀገሮችም ገበያ ለመግባት አቅጃለሁ ብሏል።
ይህን ለማድረግም ቅድመ ዝግጅቶችን አጠናቅቄያለሁ ማለቱ ተሰምቷል፡፡

ኩባንያው ወደ ሌላ ሀገር ገበያ የምሄደው ገበያውን ለመቀራመት ሳይሆን የዲጅታል መፍትሔዎች ላይ አተኩሬ በምሄድባቸው ሐገሮች መፍትሄ ለማቀበልና ገቢን ለማሳደግ አልሜ ነው ብሏል።
ይህ የተሰማው ዛሬ የኩባንያው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ የሶስት ዓመት “ቀጣይ አድማስ“ የተሰኘውን የስራ ዘመን የሚፈፅምበትን ስትራቴጂ በተመለከተ ማብራሪያ ሲሰጡ ነው፡፡
እነዚህ የትኩረት ስትራቴጂ መንገዶች 6 ምዕራፍ አላቸው ተብሏል።
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. https://www.mixcloud.com/ShegerFM/54y457/
ተህቦ ንጉሴ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyurl.com/ycxjmm3s












Comments