top of page

ነሀሴ 2 2017 - የኢትዮጵያ ባንኮች በመዋሃድ የተሻለ ካፒታልና ጉልበት እንዲኖራቸው እየተመከሩ ነው፡፡

  • sheger1021fm
  • Aug 8, 2025
  • 1 min read

የውጪ ባንኮች በኢትዮጵያ ስራ እንዲጀምሩ በሩ ከተከፈተ 3 ዓመት አለፈው፤ ግን እስካሁን ፍላጎት ካሳዩ ባንኮች በቀር ወደ ኢትዮዽያ ገብቶ ስራ የጀመረ የለም።


ይህ ስራ በባንኮች መካከል ፉክክሩን እንደሚያጠናክረው ይታመናል።


የኢትዮጵያ ባንኮች በመዋሃድ የተሻለ ካፒታልና ጉልበት እንዲኖራቸው እየተመከሩ ነው፡፡


እንዲህ ያለው አሰራርም በሌላው አለም የተለመደ ነው ሲሉ የንብ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሔኖክ ከበደ ያስረዳሉ።


በኢትዮጵያ ግን ይህ አሰራር አዲስ እንደመሆኑ እና ባንኮቹ የተለያየ ጠባይ ያላቸው በመሆኑ ምን ፈተናዎች ይኖሩታል?


መዋሃድ አለባቸው ሲባልስ እንዴት?


በሌላ በኩል ባንኮች በቁጥር አሁንም ብዙ አይደሉም ብለው እንደውም ቁጥራቸው ጨምሮ ዘርፋቸው መለያየት አለበት ብለው የሚሞግቱት ደግሞ በድሎይት አለም አቀፍ የኢንቨስትመንት አማካሪ የአፍሪካ ኢኮኖሚክስ አድቫይሰሪ ሊደርና በምስራቅ አፍሪካ የመርጅ አክዩሴሽነእ ቡድን መሪ አቶ ቴዎድሮስ ናቸው።


ለመሆኑ በየሰፈርና ቡድን ቅርጫቱ የተከፋፈሉት የኢትዮዽያ ባንኮች ይዋሀዱ ቢባልስ መንገዱ ምን ያህል እረጅምና ቀላል ሊሆን ይችላል?


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…


ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page