top of page

በኢትዮጵያ በሚሊየን የሚቆጠሩ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ላይ የሉም፡፡

  • sheger1021fm
  • 2 hours ago
  • 1 min read

ጥር 22/2018

 

በኢትዮጵያ በሚሊየን የሚቆጠሩ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ላይ የሉም፡፡

 

በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች በተፈጠረ ተፈጥሮአዊ እና ሰው ሰራሽ ችግሮች ምክንያት ወደ ትምህርት ቤት መሄድ ያለባቸው ተማሪዎች ሳይሄዱ ቀርተዋል፡፡

 

ባለፉት አመታት በነበረ አሁንም ድረስ በአንዳንድ አካባቢዎች በቀጠለ የሰላም እጦት ትምህርት ቤቶች በሙሉም ሆነ በከፊል ተጎድተዋል፤ ሰዎች ሰላምን ፍለጋ ቀያቸውን ለቀው ወጥተዋል፡፡

 

በነዚህ እና በሌሎች ምክንያች ልጆች ከትምህርት ገበታቸው እርቀዋል፡፡

 

እንደማሳያም የሰላም እጦት ከነበሩባቸው እና አሁንም ድረስ ችግሩ ከቀጠሉባቸው አካባቢዎች መካከል የሆነው አማራ ክልል የ2018 የትምህርት ዘመን ከጀመረ ወራት ማስቆጠሩ ቢታወቅም እመዘግባለው ብሎ ካቀደው ተማሪ 3 ሚሊየኑን እንዳላገኘ ተናግሯል፡፡

 

በኢትዮጵያ ባለፉት አምስት አመታት በተፈጠረ ሰላም እጦት ምክንያት በሚሊየን የሚቆጠሩ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው እርቀው ከርመዋል፡፡

 

በዚህ ምክንያት ተማሪዎቹ በተከታታይ ሁለት አመት፤ ሶስት አመት እና ከዚያ በላይ ለሚሆን ጊዜ ከመፀሀፍ እና ደብተር እርቀው የቆዩ መኖራቸውን ከክልሎቹ ሰምተናል፡፡

 

ትውልድን ለማዳን ካስፈለገ ትምህርታቸውን ያቋረጡ ተማሪዎችን ወደ ገበታቸው እንዲመለሱ ማድረግ ላይ በትኩረት መስራት ይኖርብናል ተብሏል።

 

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….

 

ፋሲካ ሙሉወርቅ

 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page