ነሀሴ 1 2017 - በኢትዮጵያ ከ71 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰዎች ጤናማ ምግብ ማግኘት እንደማይችሉ መረጃዎች ያሳያሉ
- sheger1021fm
- Aug 7
- 1 min read
በኢትዮጵያ ከ71 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ ሰዎች ጤናማ ምግብ ማግኘት እንደማይችሉ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡
የሥነ ምግብ ባለሞያዎች እንደሚሉት ከሆነ በኢትዮጵያ ከጤናማ ምግብ በተጨማሪ ሰዎች በቀን ውስጥ ማግኘት የሚገባቸውን የካሎሪ መጠን እያገኙ እንዳልሆነ ተናግረዋል።
አንድ ህጻን በቀን ውስጥ እስከ 1,600 ካሎሪ የሚያስፈልገው ሲሆን አዋቂዎች ደግሞ እስከ 2,500 ካሎሪ እንደሚያስፈልጋቸው ሰምተናል፡፡
ሆኖም በኢትዮጵያ ህፃናትም ይሁኑ አዋቂዎች ይህን ያህል ካሎሪ መጠን ያለው ምግብ ማግኘት እየቻሉ አይደለም ተብሏል፡፡
ይህ ባልሆነበት ስለጤናማ ምግብ ለማሰብ እጅግ አስቸጋሪ ነው ሲሉ የነገሩን በዓለም አቀፉ የምግብ ምርምር ፖሊሲ ተመራማሪ ሳይንቲስት የሆኑት ታደሰ ዘርፉ(ዶ/ር) ናቸው፡፡
ሰዎች ስለ ጠገቡ ብቻ ጤናማ ምግብ አግኝተዋል ማለት እንዳልሆነ ያነሱት ተመራማሪው ስለ ጤናማ ምግብና ከእሱ ጋር ተያይዘው መታየት ስላለባቸው ጉዳዮች አስረድተዋል፡፡
በአጠቃላይ በዓለም ላይ 295 ሚሊዮን ሰዎች በከፋ ምግብ ውስጥ እንደሚገኙ በተባበሩት መንግታት ድርጅት የእርሻና የምግብ ፕሮግራም ፋኦ ያወጣው ሪፖርት ይናገራል፡፡
እዚህ ቁጥር ውስጥ ኢትዮጵያን ትገኝበታለች ለዚህ እንደ ምክንያት ይነሳል ያሉትንና በሪፖርቱ የተመለከቱትን ተመራማሪውን ነግረውናል፡፡
በዚህም የእርስ በርስ ግጭት፣ የኮቪድ ወረርሽኝ፣ የአየር ንብረት ለውጥ እና የተፈጥሮ አደጋዎች ከብዙ በጥቂቶቹ ናቸው፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ……
ማርታ በቀለ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyu.com/ycxjmm3s












Comments