top of page

ታህሳስ 8፣ 2015- የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የአርብቶ አደሩና አርሶ አደሩን ስራ ለመደገፍ እስካሁን ከ9.7 ቢሊየን ብር በላይ ፋይናንስ አድርጌያለው አለ

  • Dec 17, 2022
  • 1 min read

የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የአርብቶ አደሩና አርሶ አደሩን ስራ ለመደገፍ እስካሁን ከ9.7 ቢሊየን ብር በላይ ፋይናንስ አድርጌያለው አለ።


ይንን ያህል ገንዘብ በማቅረብም በኢትዮዽያ ቀዳሚው ባንክ ሆኛለው ብሏል።


ባንኩ ከዓመታዊ ጉባኤው አስቀድሞ የሚያደርገውን የኅብረት ሥራ ማህበራት ቀንን በአዳማ አክብሯል።


የኅብረት ሥራ ማህበራት ቀኑ ለ4ኛ ጊዜ መከበሩን ከአቶ ደረጄ ወዳጆ የማህበራትና ደንበኞች ግንኙነት ዳይሬክተር ሠምተናል።


የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ ከ56 በመቶ በላይ የባንኩ ድርሻ በአርብቶና አርሶ አደሮች መያዙንና ባለቤቶቹም እነሱ መሆናቸው ተናግሯል።


በዝግጅቱ ላይ ሲነገር እንደሰማነው ባንኩ 9.7 ቢሊዮን ብር ለአርሶና አርብቶ አደሩ ስራ መደገፊያ ፋይናንስ በማድረግ በኢትዮዽያ ቀዳሚ ባንክ ሆኗል ተብሏል።


ገንዘቡ በግብርና ሜካናይዜሽን፣ በእህል፣ በቡና ምርት፣ በከብት እርባታ እና ማድለብ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለተሰማሩ ማህበራት፣ አርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች መቅረቡን ከአቶ ደረጄ ሰምተናል።


አርሶና አርብቶ አደሮች በማህበርና በዩኒየን ስር በመሆን ትልቁን የባንኩን ድርሻ እንደያዙ ተሠምቷል።


ባንኩ አንድ በመቶ ዓመታዊ ትርፉን የኅብረት ሥራ እና አርሶ አደሮችን ለማሰልጠን እንደሚያውልም ተነግሯል።


የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ በ2021/22 በጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የኅብረት ሥራ ማህበራት የተለያየ እውቅና እና ሽልማትን ተሰጥቷል።


ቴዎድሮስ ወርቁ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
ከአምስት አመት በኋላ በምግብ እጥረት ምክንያት የሚቀነጭሩ ህጻናት እንዳይኖሩ በሰቆጣ ቃል ኪዳን የገባችው ኢትዮጵያ እስካሁን በከወነችው ስራ ምን ውጤት አገኘች?

ሰኔ 15/2018 ከአምስት አመት በኋላ በምግብ እጥረት ምክንያት የሚቀነጭሩ ህጻናት እንዳይኖሩ በሰቆጣ ቃል ኪዳን የገባችው ኢትዮጵያ እስካሁን በከወነችው ስራ ምን ውጤት አገኘች? በ2025 ስራውን በ700 ወረዳዎች ላይ ተግባራዊ አደርጋለሁ ብትልም እዛ ማድረስ ግን አልቻለችም ታዲያ ከ አምስት አመት በኋላ እንደቃሏ

 
 
 
የአሜሪካው የተራድኦ ድርጅት (USAID)ን ጨምሮ የተለያዩ አለማቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ስራቸውን ማቋረጣቸው እና እርዳታ መቀነሳቸው እያሳደረ ያለው ጫና ከፍ ያለ መሆኑ ይነገራል፡፡

ሰኔ 15/2018 የአሜሪካው የተራድኦ ድርጅት (USAID)ን ጨምሮ የተለያዩ አለማቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ስራቸውን ማቋረጣቸው እና እርዳታ መቀነሳቸው እያሳደረ ያለው ጫና ከፍ ያለ መሆኑ ይነገራል፡፡ በእዚሁ ምክንያት የኢትዮጵያ ቤተሰብ መምሪያ ግማሽ ያህል ሰራተኞቹን መቀነሱን እና የሰረዘው ፕሮጅክትም መኖሩን መናገ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page