top of page

ታህሳስ 8፣ 2015- የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የአርብቶ አደሩና አርሶ አደሩን ስራ ለመደገፍ እስካሁን ከ9.7 ቢሊየን ብር በላይ ፋይናንስ አድርጌያለው አለ

  • Dec 17, 2022
  • 1 min read

የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ የአርብቶ አደሩና አርሶ አደሩን ስራ ለመደገፍ እስካሁን ከ9.7 ቢሊየን ብር በላይ ፋይናንስ አድርጌያለው አለ።


ይንን ያህል ገንዘብ በማቅረብም በኢትዮዽያ ቀዳሚው ባንክ ሆኛለው ብሏል።


ባንኩ ከዓመታዊ ጉባኤው አስቀድሞ የሚያደርገውን የኅብረት ሥራ ማህበራት ቀንን በአዳማ አክብሯል።


የኅብረት ሥራ ማህበራት ቀኑ ለ4ኛ ጊዜ መከበሩን ከአቶ ደረጄ ወዳጆ የማህበራትና ደንበኞች ግንኙነት ዳይሬክተር ሠምተናል።


የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ ከ56 በመቶ በላይ የባንኩ ድርሻ በአርብቶና አርሶ አደሮች መያዙንና ባለቤቶቹም እነሱ መሆናቸው ተናግሯል።


በዝግጅቱ ላይ ሲነገር እንደሰማነው ባንኩ 9.7 ቢሊዮን ብር ለአርሶና አርብቶ አደሩ ስራ መደገፊያ ፋይናንስ በማድረግ በኢትዮዽያ ቀዳሚ ባንክ ሆኗል ተብሏል።


ገንዘቡ በግብርና ሜካናይዜሽን፣ በእህል፣ በቡና ምርት፣ በከብት እርባታ እና ማድለብ እንዲሁም በሌሎች ዘርፎች ለተሰማሩ ማህበራት፣ አርሶ አደሮች እና አርብቶ አደሮች መቅረቡን ከአቶ ደረጄ ሰምተናል።


አርሶና አርብቶ አደሮች በማህበርና በዩኒየን ስር በመሆን ትልቁን የባንኩን ድርሻ እንደያዙ ተሠምቷል።


ባንኩ አንድ በመቶ ዓመታዊ ትርፉን የኅብረት ሥራ እና አርሶ አደሮችን ለማሰልጠን እንደሚያውልም ተነግሯል።


የኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ በ2021/22 በጀት ዓመት የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ የኅብረት ሥራ ማህበራት የተለያየ እውቅና እና ሽልማትን ተሰጥቷል።


ቴዎድሮስ ወርቁ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
የኤሌክትሪክ ታሪፍ በየጊዜው ሲጨምር ይታያል፡፡

ነሐሴ 7 2018 የኤሌክትሪክ ታሪፍ በየጊዜው ሲጨምር ይታያል፡፡ በዚህም ደንበኞች ቅሬታ ያቀርባሉ ፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በበኩሉ አዲስ የታሪፍ ጭማሪ አለማድረጉን፤ የአሁኑ የዋጋ ለውጥ ከ2017 ጀምሮ በ16 ዙር ለማስፈጸም የታቀደው አሰራር አካል ነው ብሏል፡፡ እንደውም ከሁለት አመት በፊት ተግባራዊ ያ

 
 
 
ዛሬ ብሔራዊ ባንክ ይፋ ባደረገው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ በ161 ብር ከ79 ሳንቲም መሸጡ ተነገረ፡፡

ነሐሴ 6 2018 ዛሬ ብሔራዊ ባንክ ይፋ ባደረገው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ በ161 ብር ከ79 ሳንቲም መሸጡ ተነገረ፡፡ ዛሬ ይፋ በሆነው ጨረታ 125 ሚሊዮን ዶላር ለጨረታ ቀርቧል ተብሏል፡፡ በጨረታው 28 ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን በጨረታው የድርሻቸውን ተጫርተው የወሰዱ ባንኮች ቁጥር 9 መሆ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page