top of page

ዛሬ ብሔራዊ ባንክ ይፋ ባደረገው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ በ161 ብር ከ79 ሳንቲም መሸጡ ተነገረ፡፡

  • 1 day ago
  • 1 min read

ነሐሴ 6 2018


ዛሬ ብሔራዊ ባንክ ይፋ ባደረገው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ አንድ የአሜሪካ ዶላር በአማካይ በ161 ብር ከ79 ሳንቲም መሸጡ ተነገረ፡፡


ዛሬ ይፋ በሆነው ጨረታ 125 ሚሊዮን ዶላር ለጨረታ ቀርቧል ተብሏል፡፡


በጨረታው 28 ባንኮች የተሳተፉ ሲሆን በጨረታው የድርሻቸውን ተጫርተው የወሰዱ ባንኮች ቁጥር 9 መሆናቸው ተነግሯል፡፡


ለጨረታው የቀረበው ከፍተኛው ገንዘብ 163 ብር ከ98 ሳንቲም ሲሆን ዝቅተኛው 159 ብር ከ98 ሳንቲም ሆኗል፡፡


ዛሬ ይፋ በሆነው የውጭ ምንዛሬ ጨረታ 125 ሚሊዮን ዶላር መቅረቡን ይፋ ያደረገው ብሔራዊ ባንክ ቀጣዩን የጨረታ ጊዜም በፕሮግራሙ መሰረት ይፋ አደርጋለው ብሏል፡፡


ዛሬ ይፋ በሆነው ጨረታ ላይ የቀረበው የውጭ ምንዛሬ መጠን 125 ሚሊየን ዶላር ቢሆንም በባንኮቹ በኩል የቀረበው ፍላጎት ግን 470.17 ሚሊየን ዶላር መሆኑ ይፋ ተደርጓል።


ቴዎድሮስ ወርቁ

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page