top of page

ታህሳስ 6፣ 2015- የሴኔጋል መንግስታዊ የኮሮና ቫይረስ መከላከያ ገንዘብ ለምዝበራ እና ብልሹ አሰራር የተጋለጠ ነበር ተባለ


የሴኔጋል መንግስታዊ የኮሮና ቫይረስ መከላከያ ገንዘብ ለምዝበራ እና ብልሹ አሰራር የተጋለጠ ነበር ተባለ፡፡


የአገሪቱ የኮሮና ቫይረስ መከላከያ ገንዘብ ለምዝበራ፣ ለብልሹ አሰራር እና ለብክነት መጋለጡን ደርሼበታለሁ ያለው የሂሳብ አጣው መስሪያ ቤት እንደሆነ አፍሪካ ኒውስ ፅፏል፡፡


የአገሪቱ የፍትህ ሚኒስቴር አስፈላጊውን እርምጃ ይወስድ ዘንድ አበክሮ መጠየቁ ተሰምቷል፡፡


የሂሳብ አጣሪ መስሪያ ቤት ለኮሮና ቫይረስ መከላከያው ከተመደበው ገንዘብ የብዙ ሚሊዮን ዩሮ ግምት ያለው ምዝበራ መፈፀሙን አረጋግጧል ተብሏል፡፡


ምዝበራው የተፈፀመው በምርቶች እና በሸቀጦች ግዢ የተጋነነ ክፍያ እንደሆነ ዘገባው አስታውሷል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

bottom of page