top of page

ታህሳስ 17፣ 2015- ሶማሊያ ውስጥ በአልሸባብ ፅንፈኛ ቡድን ታግተው የቆዩ 14 ኢራናዊያን ዓሣ አስጋሪዎች ተለቀው አገራቸው መግባታቸው ተሰማ

  • sheger1021fm
  • Dec 26, 2022
  • 1 min read

ሶማሊያ ውስጥ በአልሸባብ ፅንፈኛ ቡድን ታግተው የቆዩ 14 ኢራናዊያን ዓሣ አስጋሪዎች ተለቀው አገራቸው መግባታቸው ተሰማ፡፡


ኢራናውያኑ ዓሣ አስጋሪዎች ለ8 ዓመታት በአልሸባብ ታግተው መቆየታቸው ታስም የወሬ ድርጅት አስታውሷል፡፡


ዓሣ አስጋሪዎቹ የተለቀቁት የኢራን መንግስት ባደረገው ብርቱ ድርድር ነው ተብሏል፡፡


ከ8 ዓመታት በፊት በኢራናውያኑ ዓሣ አስጋሪዎች ላይ እገታው ተፈፅሞቸው የነበረው በአለም አቀፍ የባህር መስመር ላይ እንደነበር ዘገባው አስታውሷል፡፡


የሶማሊያ መንግስት ጦር ከአልሸባብ ፅንፈኛ ቡድን ጋር ሲዋጋ ከ15 አመታት በላይ ሆኗታል፡፡


በአሁኑ ወቅትም ፅንፈኛውን ቡድን ለመደምሰስ መጠነ ሰፊ ዘመቻ እያደረገ መሆኑ ይነገራል፡፡


የኔነህ ከበደ


ሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

https://bit.ly/33KMCqz

コメント


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page