top of page

ታህሳስ 10፣2016 -የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳልፏል

  • Dec 20, 2023
  • 1 min read

የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበትን፣ ካሣ የሚከፈልበትን እና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ሁኔታ ለመወሰን የቀረበው ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ አንዱ ነው፡፡


ካሣን የመተመን፣ የመክፈልና ተነሺዎችን መልሶ የማቋቋም ኃላፊነት የተጣለባቸውን አካላትና ግዴታዎቻቸውን ግልጽ ማድረግ በማስፈለጉ ማሻሻያው መዘጋጀቱ ተነግሯል።


የሜዳይ፣ ኒሻን እና ሽልማት ረቂቅ አዋጅም በምክር ቤቱ ውይይት ተደርጎበታል።


የሕዝብ በዓላትን፣ የዕረፍት ቀናትን እና የበዓላትን አከባበር ለመወሰን በቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ እንዲሁ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውይይት አካሂዷል።


በሶስቱ ረቂቅ አዋጆች ላይ ምክር ቤቱ ከተወያየ በኋላ ግብዓቶችን በማከል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፉ በሙሉ ድምጽ ወስኗል።


የአምራች ኢንዱስትሪ ረቂቅ ፖሊሲ ደግሞ ከጸደቀበት ቀን ጀምሮ በስራ ላይ እንዲውል ነው የወሰነው።


መረጃው የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ነው።


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ… https://bit.ly/33KMCqz

Recent Posts

See All
የሐምሌ 18 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ስፔን በስፔኗ ርዕሰ ከተማ ማድሪድ አቅረቢያ ነዋሪዎች በመዛመት ላይ በሚገኘው ከባድ የሰደድ እሳት ምክንያት ለቅቀው እንደወጡ ታዘዙ፡፡ የማድሪድ ምዕራባዊ ክፍል አቅራቢያ የሰደድ እሳቱ በጣሙን ያየለበት እንደሆነ ቢቢሲ ፅፏል፡፡ እስከ ትናንት ምሽትም ከ19 ሺህ በላይ ሰዎች ለቀው መውጣታቸው ተጠቅሷል፡፡ በስፔን ወቅታ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page