''ተቋማት ብክነት ከበዛው መንገድ መውጣት አለባቸው'' የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት
- sheger1021fm
- 2 hours ago
- 1 min read
ጥር 15/2018
የተቋማት የሀብት ብክነት የሚበዙት የኢትዮጵያ ተቋማት ችግር ነው ተባለ፡፡
ተቋማት ከዚህ ብክነት የበዛው መንገድ መውጣት አለባቸው ሲልም የኢትዮጵያ ጥራት ሽልማት ድርጅት ተናግሯል፡፡
የሽልማት ድርጅቱ ተቋማት የሰው ኃይል በማሰልጠን እና ለስራ ብቁ በማድረግ ዙሪያ የሚሰሩ ቢሆንም ያመጡትን ውጤት ግን በደንብ መገምገም ይኖርባቸዋል ብሏል።

የተቋማትን ጥራት ደረጃ በምመዝንበት እና በማወዳድርበት ወቅት ከሀብት ብክነት ጋር የተገናኘ ችግር ደጋግሞ እየገጠመኝ ነው ብሏል።
እንደየ ተቋማቱ የተለያዩ ጠንካራና ደካማ ጎኖች እንዳሉም ተነግሯል።
በውድድሩ ከተሳተፉ ተቋማት ውስጥ ሌላኛው ክፍተት ሆኖ የተገኘው አንዳንድ ተቋማት የሰው ኃይል ብቻ ማሰልጠን እንደ ዋነኛ ግብ አድርጎ መቁጠር ነውም ብሏል።
የተቋማትም ልህቀት የሚለካው በዚህ ብቻ አይደለም ፤ ይሄ ሊስተካከል ይገባል ብሏል ።
የሽልማት ድርጅቱ ተቋማትን ለማወዳደር በተለያዩ የሚዲያ አማራጮች ጥሪ ባደርግም በውድድሩ የሚሳተፉት ግን በጣም ጥቂት ናቸውም ሲል ተናግሯል ።
ሙሉ ዘገባወን ያድምጡ…
ፍቅሩ አምባቸው
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…..
YouTube : https://url-shortener.me/2DTR
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://url-shortener.me/2DTY
WhatsApp :https://url-shortener.me/2DU0
Website፡ https://www.shegerfm.com/
LinkedIn :https://url-shortener.me/2DU8
Tiktok : https://url-shortener.me/2DUB
Instagram : https://url-shortener.me/2DUD












Comments