top of page

ተላላፊ ያልሆኑ ህመሞች በኢትዮጵያ በሚከሰቱ ሞቶች ከግማሽ በላይ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑንን ጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡

  • sheger1021fm
  • 25 minutes ago
  • 1 min read

ህዳር 12 2018

 

ተላላፊ ያልሆኑ ህመሞች በኢትዮጵያ በሚከሰቱ ሞቶች ከግማሽ በላይ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑንን ጤና ሚኒስቴር ተናግሯል፡፡

 

የኩላሊት ህመተኞችን በተመለከተ የወጣውን መመሪያ ተግባራዊ ለማድረግ ስራዎች መጀመራቸውን ሰምተናል፡፡

 

እየጨመሩ ካሉ ተላላፊ ያልሆኑ ህመሞች መካከል የስኳር በሽታ፣ የደም ግፊት፣ ስትሮክ፣ ኩላሊት፣ የልብና የደም ስር መዘጋት እንዲሁም የአዕምሮ መታወክና ካንሰር ከብዙ በጥቂቶቹ መሆናቸውን ሚኒስቴሩ ተናግሯል፡፡

 

ree

በተለይም የደም ግፊት ከፍተኛ ለሆነ የኩላሊት በሽታ እያጋለጠ እንደሆነና በዚህም 6 በመቶ የሚሆኑ ሰዎች ስር ለሰደደ የኩላሊት ህመም አንደሚጋለጡ በጥናት መረጋገጡን የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ደረጄ ዱጉማ ነግረውናል፡፡

 

ሚኒስትር ዴኤታው ይህንን ያሉት ስር የሰደደ የኩላሊት ህመምን ለማከም የቅድመ ምርመራ ለመከወን እንዲሁም የጤና ባለሞያዎችን ለማብቃት የወጣውን መመሪያ ለማብሰር እና የዚሁ አካል ከሆኑት ከPSI ኢትዮጵያ እና አስትራ ዜኒካ ከተባሉ ግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ጋር አብሮ ለመስራት በተወያዩበት ወቅት ነው፡፡

 

ሙሉ ዘገባውን ለማድመጥ….

 

ማርታ በቀለ

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇

 

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page