ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ሐዋርያዊ ኃላፊነታቸውን አስረከቡ።
- 7 hours ago
- 1 min read
ሰኔ 5/2018
የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀጳጳስ እና የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ሐዋርያዊ ኃላፊነታቸውን አስረከቡ።
ብፁዕ ካርናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ኃላፊነታቸውን ያስረከቡት በጡረታ ምክንያት እንደሆነ ቤተክርስቲያኗ አስታውቃለች፡፡
የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዎ 14ኛ ብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ላቀረቡት ከሃላፊነት የመነሳት ጥያቄ፤ በዛሬው ዕለት መቀበላቸውን በቅድስት መንበር ልዩ መልዕክተኛ ብፁዕ ካርዲናል ክላውዲዮ አማካይነት ይፋ መደረጉን በቤተክርስቲያኗ መግለጫ ላይ ተጠቅሷል፡፡

የብፁዕ ካርዲናል አቡነ ብርሃነ ኢየሱስ ተተኪ በመሆን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ረዳት ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ተስፋስላሴ የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ሊቀጳጳስ ሆነው ተሹመዋል።
ንጋቱ ሙሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i





Comments