‘’በየቦታው ላለው መሬትና ለሚዘራው ሰብል የሚስማማ ማዳበርያ ለማቅረብ የሚያስችል ጥናት እየተደረገ ነው’’
- sheger1021fm
- 2 hours ago
- 1 min read
ጥር 26/2018
ኢትዮጵያ ውስጥ በየቦታው ላለው መሬትና ለሚዘራው ሰብል የሚስማማ ማዳበርያ ለማቅረብ የሚያስችል ጥናት እየተደረገ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናገሩ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ያሉት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 10ኛ መደበኛ ስብሰባ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በተካሄደበት ወቅት ነው፡፡
ከዚህ ቀደም ለሁሉም ሰብል ዓይነትና መሬት ይቀርብ የነበረው ማዳበሪያ ተመሳሳይ ነበር ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ይህን ለመቀየር መንግስት እየሰራ ነው ብለዋል፡፡
ጥናቱ ሲጠናቀቅና ወደ ስራ ሲገባ አሁን ያለው ምርት በእጥፍ እንደሚያድግም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ለምክር ቤት አባላቱ ተናግረዋል፡፡
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7








