top of page

በአዲስ አበባ በ3 ወራት ውስጥ ከ25,000 በላይ ህፃናት ተወልደው፣ የልደት ምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል፡፡

  • sheger1021fm
  • Nov 5, 2025
  • 1 min read

ጥቅምት 26 2018


በአዲስ አበባ በ3ወራት ውስጥ ከ25,000 በላይ ህፃናት ተወልደው፣ የልደት ምስክር ወረቀት ተሰጥቷቸዋል፡፡


በአዲስ አበባ ከተማ በወቅቱ የልደት ምዝገባ ያደረጉ ህጻናት ቁጥር ከ25,000 በላይ መሆኑን የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ጥጋቡ ሹመይ ነግረውናል፡፡


ጋብቻ ከ2,500 በላይ፣ ፍቺ 853 ፣ ሞት 1,258 ፣ ጉዲፈቻ ደግሞ 58 በአጠቃላይ 30,500 ኩነቶች ባጋጠሙ በወቅታቸው መመዝገባቸውን ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡

በአጠቃላይ በበጀት ዓመቱ 3 ወራት በወቅቱ በዘገየና ጊዜ ገደቡ ባለፈ 172,011 ወሳኝ ኩነቶች መመዝገባቸውን ከኤጀንሲው ሰምተናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…

ማርታ በቀለ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

👇👇👇


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page