በንጋት ሀይቅ እስከ 25,000 ሄክታር መሬት በመስኖ ማልማት ይቻላል ተባለ
- sheger1021fm
 - 22 hours ago
 - 1 min read
 
ጥቅምት 24 ቀን 2018 ዓ.ም
የህዳሴውን ግድብ ተከትሎ በተፈጠረው ንጋት ሀይቅ እስከ 25,000 ሄክታር መሬት በመስኖ ማልማት ይቻላል ተባለ፡፡
የህዳሴውን ግድብ ከኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጫነት ጋር ብቻ ተገናኝቶ እንዲነሳ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት ይፈልጋሉ ተብሏል።
በግድቡ የድርድር ወቅትም ለሀይል ማመንጫ ብቻ የሚል ውልን ኢትዮጵያ እንድትፈርም በተደጋጋሚ ትጠየቅ እንደነበርም ተነግሯል።

የህዳሴው ግድብና እሱን ተከትሎ የተፈጠረው ንጋት የሰው ሰራሽ ሃይቅ ግን ለኢትዮጵያ ከሀይል ማመንጫ በላይ የመስኖም፣ የዓሣ ምርትም እንዲሁም የቱሪዝም መዳረሻም ጭምር ነው ተብሏል።
ኢትዮጵያ በጥናት እየለየች በሀይቁ ዙሪያ የመስኖ እርሻን ማስፋፋት እንዳለባት ያነሱት የግድቡ መሪ ተደራዳሪ የነበሩት ስለሺ በቀለ (ዶ.ር) እስከ 25 ሺህ ሄክታር መሬትንም በዙሪያው ማልማት ይቻላል ብለዋል።
ቀጣዩ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ትልቁ ፕሮጀክትም መስኖን በሀገር አቀፍ ደረጃ ማስፋፋት መሆን አለበት ተብሏል።
ኢትዮጵያን ይህንን እንድትጠቀምበት ተጠይቋል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..
ቴዎድሮስ ወርቁ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s








