በትምህርት ዘርፍ ላይ የሚደረገው ለውጥ ህብረተሰቡን ያሳተፈ አይደለም የሚል ጥያቄ እየተነሳ ነው መሆኑ ተነገረ፡፡
- sheger1021fm
- 3 hours ago
- 1 min read
ታህሳስ 9/2018
በትምህርት ዘርፍ ላይ የሚደረገው ለውጥ ህብረተሰቡን ያሳተፈ አይደለም የሚል ጥያቄ እየተነሳ ነው መሆኑ ተነገረ፡፡
ይህ ሃሳብ የተነሳው ስለ ትምህርት እናውጋ ማህበር ባደረገው ውይይት ላይ ነው፡፡
በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የሥነ ትምህርት እና የቋንቋዎች ኮሌጅ ባልደረባ የሆኑት ዶክተር ካሣ ሚካኤል ስለትምህርት እናውጋ ማህበር በተደጋጋሚ ኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው የትምህርት ችግር በተመለከተ መመካከራቸውን ጠቅሰዋል፡፡
እነዚህ ማህበርተኞች በቅርቡ በብሪቲሽ ካውንስል በመገናኘት ባለፉት ጊዜያት የተወያዩባቸው ዋነኛ ጉዳዮችን የያዘ ሰነድ አሰናድተው ይፋ አድርገዋል፡፡
የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ተማሪዎች የተማሪ ወላጆችና ሌሎችም አጋር አካላት አሉበት የተባለው ይህ ማህበር አሁን ስላለው የትምህርት ዘርፍ ችግር ጣት መጠቋቆም ለውጥ ሊያመጣ ስለማይችል ለችግሮቹ መፍትሄ ለማመልከት እና የራሱን ሀላፊነት ለመወጣት በማሰብ ምክክሮቹን እንደሚያደርግ ሰምተናል፡፡
ካሣ ሚካኤል(ዶ/ር) እንደሚሉት ትምህርት ወድቋል ብሎ መናገር ለውጥ አያመጣም መፍትሄው በመተጋገዝ ከወደቀበት ማንሳት ነው ይላሉ፡፡
የተዘጋጀው ሰነድ ለውይይት መነሻ ሀሳብ ይሆናል በማለት የተሰናዳ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ነገር ግን በትምህርት ዘርፍ ለተጋረጡ ችግሮች ዋነኛ መፍትሄ ይሆናል በሚል የተዘጋጀ አለመሆኑን አብራርተዋል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…
በረከት አካሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1








