በባንኮችና በሌሎችም ዘርፎች እንደተደረገው ለውጭ አየር መንገዶች ዘርፉን የመክፈት ፍላጎት መንግስት ለጊዜው የለውም ተባለ፡፡
- 2 hours ago
- 1 min read
የካቲት 16/2018
በባንኮችና በሌሎችም ዘርፎች እንደተደረገው ለውጭ አየር መንገዶች ዘርፉን የመክፈት ፍላጎት መንግስት ለጊዜው የለውም ተባለ፡፡
በኢትዮጵያ የሚሰሩ የግል አየር መንገዶች ብዛት 12 ቢደርስም እነደ ኬኒያ እና ኡጋንዳ ካሉት የጎረቤት ሀገራት ጋር ሲነፃፀር ግን በአቅምም በቁጥርም ዝቅተኛ ነው ይባላል። እነዚህ የግል አየር መንገዶች(General Aviation) ዘርፉ ጠንክሮና እራሱን ችሎ መቆም እስከሚችል ድረስም መንግስት የውጭ ሀገር አየር መንገዶችን የመጋበዝ ፍላጎት የለውም ተብሏል።
የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ ዮሃንስ አበራ እንደነገሩን በሂደት ግን በሩ ለውጭ ባለሃብቶች ክፍት መሆኑ አይቀርም።

በኢትዮጵያ በግል አየር መንገድ የተሰማሩ ኩባንያዎች ከህግ እስከ አሰራር የሚያነሷቸው ብዙ ችግሮች እንዳሉ ይነሳል። ዋና ዳይሬክተሩ የሚበዙት ችግሮች በሂደት እየተፈቱ መሆኑን ጠቅሰው እንደ ምሳሌም አውሮፕላንን መያዣ አድርጎ ከባንክ ገንዘብ መበደር የተፈቀደው በቅርብ ጊዜ መሆኑን አንስተዋል። ሌሎች ተመሳሳይ የዘርፉ ችግሮችም እየተፈቱ ነው ብለዋል።
በቅርብ ጊዜ ውስጥም ተጨማሪ ሁለት ኩባንያዎች በግል የአቪዬሽን ዘርፍ ለመግባት በዝግጅት ላይ መሆናቸውንም ነግረውናል።
በተለይ አንደኛው አውሮፕላኖችን እያስመጣ በአፍሪካ ሀገራት እያከራየ ለመስራት በዝግጅት ላይ ነው ተብሏል።
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ……
ቴዎድሮስ ወርቁ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7

