በበጀት ዓመቱ ሰባት ወራት ከ800 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናግረዋል።
- sheger1021fm
- 1 hour ago
- 1 min read
ጥር 26/2018
በበጀት ዓመቱ ሰባት ወራት ከ800 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መሰብሰቡን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ተናግረዋል።
በአጠቃላይ በጀት ዓመቱ 1 ነጥብ 2 ቢለየን ብር ገቢ ለመሰብሰብ እንደታቀደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት አባላት ማብራሪያ ሲሰጡ ተናግረዋል።
የሰባት ወራቱ አፈጻጸም የዓመቱ ዕቅድ ቀድሞ እንደሚሳካ የሚያመለክት ነው ብለዋል።
ያለውን አፈጻጸም ተከትሎ በፌዴራል ደረጃ የተቀመጠውን የ1 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ዕቅድ ወደ 1 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር የማሳደግ ሃሳብ እንዳለ ጠቅሰዋል።

ክልሎች የሚሰበስቡትን ገቢ ደግሞ 1 ትሪሊየን ብር እንዲደርስ መታሰቡን አመልክተዋል።
በዚህም በአጠቃላይ 2 ነጥብ 5 ትሪሊየን ብር በመሰብሰብ ከአጠቃላይ ጥቅል ሀገራዊ ምርት ወይም ጂ ዲ ፒ ዘጠኝ በመቶ ድርሻ የሚይዝ ገቢ እንዲኖረን እየሰራን ነው ሲሉ አክለዋል።
ኢትዮጵያ እስከ አሁን የምትሰበስበው ገቢ ከአጠቃላይ ጥቅል ሀገራዊ ምርት ወይም ጂ ዲ ፒ ድርሻው ሰባት በመቶ እንደሆነ ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስታውሰዋል።
የታክስ መሰረትን መስፋት እና ኦቶሜሽን ላይ የተሰራው ስራ የሚሰበሰበው ገቢ እንዲያድግ አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ ስድስት ወራት መንግስት 801 ቢሊየን ብር ወጪ ያደርጋል ተብሎ ታቅዶ እንደነበር ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወጪ የሆነው ግን የዕቅዱ 48 ነጥብ 5 በመቶ ነው ብለዋል።
ንጋቱ ረጋሳ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7








