top of page

በሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ርቀው ቆይተዋል፡፡

  • sheger1021fm
  • 2 hours ago
  • 1 min read

ጥር 25/2018

 

በሰው ሰራሽ እና ተፈጥሯዊ ምክንያቶች ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ርቀው ቆይተዋል፡፡

 

በኢትዮጵያ በሚሊየን የሚቆጠሩ ተማሪዎች ለተከታታይ 3 ዓመታት እና ከዚያ በላይ ለሚሆን ጊዜ ከትምህርት ገበታቸው ላይ አልነበሩም፡፡

 

በተለይ በአንዳንድ የሀገሪቱ አካባቢዎች በነበሩ አሁንም ድረስ በቀጠሉ የሰላም እጦቶች ተማሪዎች ቀያቸውን ለቀው ወጥተዋል፣ ትምህርት ቤቶች በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ወድመዋል፡፡

 

በዚህም ምክንያት ልጆች ከእስክርቢቶ እና ደብተር እርቀው ሰንብተዋል፤ በሚሊየን የሚቆጠሩ ተማሪዎችም ከትምህርት ቤት በራፍ ሳይደርሱ ከርመዋል፡፡

 

ልጆች ከትምህርት ገበታ መራቃቸው ሊያገኙት የሚገባቸውን እውቀት እና ሊያውቋቸው የሚገቡ ነገሮችን ይነፈጋሉ ይህ ደግሞ በተለያየ መንገድ ተፅእኖውን ያበረታዋል ተብሏል፡፡

 

በሀገር አቀፍም ሆነ በግለሰብ ደረጃ ሊያስከትለው የሚችለው ችግር ቀላል የሚባል እንዳልሆነ የሚነገር ሲሆን ጉዳቱን አሁንም እየተመለከትነው ነው ተብሏል።

 

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…..  

 

ፍቅሩ አምባቸው

 

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

YouTube : https://shorturl.at/18TS1                   

 

 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page