top of page

በሀገር አቀፍ የምክክር ጉባዔ ላይ የሚመከርባቸው አጀንዳዎች መሰረታዊ የሆኑ 10 ጉዳዮች ላይ ነው ተባለ።

  • 3 hours ago
  • 1 min read

ሰኔ 13/2018


በሀገር አቀፍ የምክክር ጉባዔ ላይ የሚመከርባቸው አጀንዳዎች መሰረታዊ የሆኑ 10 ጉዳዮች ላይ ነው ተባለ።


ይህን ያሉት የምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር መሀመድ ድሪር ዛሬ ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም በቢሾፍቱ ከተማ ከመገናኛ ብዙሃን የስራ ሃላፊዎች እና ጋዜጠኞች ጋር ወይይት በተደረገበት ወቅት ነው።


በውይይት መድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ካደረጉት መከካል አንዱ የሆኑት ኮሚሽነር አምባሳደር መሀመድ ድሪር ናቸው።


አምባሳደሩ የምክክር ጉባዔው ሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም እንደሚጀመር አስታውሰዋል።


ጉባዔው የሚካሄደው ደግሞ በ10 መሰረታዊ አጀንዳዎች ላይ ነው ሲሉ አስረድተዋል።

አጀንዳዎቹ ምን ምን እንደሆኑ ወደፊት ለህዝብ እንደሚገለፅ ጠቁመዋል።


ለኢትዮጵያ ይህ ምክክር ምትክ የለውም ፣ ሂደቱ ከምንም ጋር የሚወዳደር አይደለም ያሉት ደግሞ ኮሚሽነር መላኩ ወልደማሪያም ናቸው።


"በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት፣ ወደፊትም ከሚመጡት ፕሮጀክቶች ሁሉ ሀገራዊ ምከክሩ የሚበልጠው የለም" ሲሉ አስረድተዋል።


ይህን እድል አለመጠቀም በታሪክ ሊጸጽትን ይችላል ሲሉም አክለዋል።


እድሉ አንዳያመልጠን መጠቀም አለብን፤ ይህ የመንግስት ጉዳይ፣ የኮሚሽነሮቹ ጉዳይ ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ ጉዳይ ነው ብለዋል።


ሐምሌ 8/2018 የሚጀምረውን የሀገራዊ ምክክር ዋና የምክክር መድረክን የመገናኛ ብዙሃን በሀላፊነትና ምክክሩ እንዲሳካ ገንቢ በሆነ መንገድ እንዲዘግቡ በውይይቱ ወቅት ተጠይቋል።


ያሬድ እንዳሻው


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page