top of page

ሰኔ 6 2017 - ለመጪው ረቂቅ በጀት አዲስ አበባ ለመጀመሪያ ጊዜ በጀት ሳይደለደልላት ቀርቷል

  • Jun 13, 2025
  • 1 min read

ለመጪው በጀት ዓመት ለክልሎች መደገፊያ ከተያዘው በጀት ከፍተኛውን የሚይዘው ኦሮሚያ ሲሆን ከ108.4 ቢሊየን ብር በላይ ተመድቦለታል፡፡


#አዲስ_አበባ በረቂቅ በጀቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በጀት ሳይደለደልላት ቀርቷል፡፡


የፌዴራል መንግስቱ ለክልሎች መደገፊያ ከያዘው በጀት በሁለተኛ ደረጃ የአማራ ክልል ድርሻውን የሚይዝ ሲሆን 67.9 ቢሊየን ብር ተደልድሎለታል፡፡


በሶስተኛ ደረጃ ሶማሌ ክልል 31.4 ቢሊየን ብር እንዲሁም ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በ22 ቢሊየን ብር 4ኛውን ደረጃ ይዘዋል፡፡


ትግራይ ክልል 18.9 ቢሊየን ብር እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል 18.5 ቢሊየን ብር በጀት የተያዘላቸው ናቸው፡፡


ሲዳማ ክልል 12.9 ቢሊየን ብር፣ ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያና አፋር ክልል ተቀራራቢ ከ9.5 ቢሊየን ብር በላይ በጀት የተመደበላቸው ናቸው፡፡


ቀሪዎቹ ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል በስተቀር ማለትም ሐረሪ፣ ጋምቤላ እና ድሬደዋ ከተማ አስተዳደር ከ5 ቢሊየን ብር በታች የተመደበላቸው መሆኑ ከረቂቅ በጀቱ ተመልክተናል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከከዚህ ቀደሙ በተለየ ሁኔታ በዚህ አመት በረቂቅ በጀቱ አልተካተችም፤ ምክንያቱ ምን እንደሆነም በረቂቅ በጀቱ ላይ አልተጠቀሰም፡፡


ትዕግስት ዘሪሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





Recent Posts

See All
በኢትዮጵያ እያንዳንዱ ብሄረሰብ የራሱን ታሪክ ብቻ ለይቶና አጉልቶ የሚያቀርብበት ስርዐት መቀየር እንዳለበት የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ተናገሩ ።

ሐምሌ 23 2018 በኢትዮጵያ እያንዳንዱ ብሄረሰብ የራሱን ታሪክ ብቻ ለይቶና አጉልቶ የሚያቀርብበት ስርዐት መቀየር እንዳለበት የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ተናገሩ ። በኢትዮጵያ የብሄረሰቦች ታሪክ ጥልቅ ትስስር እና መስተጋብር ያለው ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የታሪክ ባለሞያዎች ማህበር ከላይፍ ኤንድ ፒስ ኢንስ

 
 
 
በ2018 በጀት ዓመት ከ1.2 ቢሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

ሐምሌ 23 2018 በ2018 በጀት ዓመት ከ1.2 ቢሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። በየዓመቱ በሀገሪቱ የሚገኘው የምርት መጠን እያደገ እንደሚመጣ ሪፖርቶች ያመልክታሉ። በገበያው ውስጥ ግን የምርት ዋጋ ከአመት አመት እየጨመረ እንጂ ሲቀንስም አይታይም። ይህ ለምን ሆነ? እውነትስ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page