top of page

ሰኔ 18 2017 - ምጣኔ ሐብት - የማክሮ ኢኮኖሚ ስርዓት ለውጡ

  • sheger1021fm
  • 23 hours ago
  • 1 min read

የኢትዮጵያ የውጭ ምንዛሪ ገበያው፤ ሽያጭ ልዋጩ በሶስት የተከፈለ ነው።


አንደኛው መደበኛው በባንኮች የሚከናወነው የየእለት ምንዛሪ ገበያ ነው።


ሁለተኛው ፍቃድ ያገኙት ስድስቱ የግል የውጭ ምንዛሪ ገዥ እና ሻጭ የፎርኤክስ ቢሮዎች ናቸው።


ሦስተኛው በጥቁር ኢኮኖሚ አንገት ለአንገት የኢትዮጵያን የውጭ ምንዛሪ ገበያን በመረበሽ ተያይዞ የነበረው የትይዩ የውጭ ምንዛሪ በረንዳ ነው።


ሐገር ይህን ለማስታገስ ብላ በማዕከላዊ ባንክ በየጊዜው የሚደረገው ጥብቅ የውጭ ምንዛሪ አስተዳደርና መመሪያ እያወጣ እየተገበረ ነው።


በእርግጥ ለትርፍ የተቋቋሙት ባንኮች ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እዳ እና ጫና ቢኖርባቸውም እንዴት በውጭ ምንዛሪ ሽያጭና ግዥ ትርፋቸው ከፍተኛ ይሆናል ተብለው ይተቻሉ።


የማዕከላዊ ባንኩን ጥብቅ አሰራር እና የብር የመግዛት አቅም ውሳኔ ተከትሎ አርጩሜውን ላለመቅመስም ወደኋላ ሲሉ ይታያል።


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ……


ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





Comentários


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page