ሚያዝያ 16፣2016 - በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ላይ የተነሳው እሳት ሙሉ ለሙሉ መጥፋቱ ተነግሯል
- sheger1021fm
- Apr 24, 2024
- 1 min read
ሚያዝያ 10/ 2016 በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ላይ የተነሳው እሳት ሙሉ ለሙሉ መጥፋቱ ተነግሯል።
በተለያዩ አካላት ርብርብ እሳቱን ከትናንት በስትያ ምሽት ላይ መቆጣጠር እንደተቻለ የነገሩን የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ኤፍሬም ወንድዬ ናቸው።
በፓርኩ ውስጥ ባለው ተቀጣጣይ ክምችት ተዳፍኖ የቀረ እሳት ካለ በሚል የአሰሳ ስራ እየተሰራ ይገኛልም ብለዋል።

ስለ እሳቱ መነሻ ምክንያት ለማወቅ ማጣራት እየተካሄደ ነው ያሉን አቶ ኤፍሬም ከዚሁ ጋር በተገናኘ ተጠረጥረው የተያዙ ሰዎች ግን እንዳሉ ነግረውናል፡፡
ፓርኩን ህብረተሰቡ በእኔነት ስሜት እንዲጠብቀው በማድረግ ዘላቂ የሆነ የእሳት መከላከል ስራ እንሰራለን የሚሉት ሃላፊው፤ ጥያቄ እያስነሱብን ላሉ የዝግጅት ስራዎችም ምላሽ መስጠት እንዳለብን ተረድተናል ብለዋል።
የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ 412 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ያለው ሲሆን እንደ ዋልያ፣ ቀይ ቀበሮ እና ጭላዳ ዝንጀሮ ያሉ ብርቅዬ የዱር እንስሳት መገኛ መሆኑ ተነግሯል።
ንጋቱ ረጋሣ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Telegram: @ShegerFMRadio102_1
Youtube: http://tiny.cc/ShegerFM1021Radio
Website: https://www.shegerfm.com/
Tiktok: https://bit.ly/44Dd6Il












If you arouse sexual passion in the hills, then our Call Girls in Manali are the best matches for you. Besides, they are competent to offer sensual GFE, classy companionship, and giving you a feeling of total relaxation and pleasure while on your trip. If you happen to be a solo traveler and want some private fun, then these gorgeous beauties are the ones who really understand how to delight you.