top of page

ሚያዝያ  16፣2016 - በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ላይ የተነሳው እሳት ሙሉ ለሙሉ መጥፋቱ ተነግሯል

  • Apr 24, 2024
  • 1 min read

ሚያዝያ 10/ 2016 በሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ላይ የተነሳው እሳት ሙሉ ለሙሉ መጥፋቱ ተነግሯል።

 

በተለያዩ አካላት ርብርብ እሳቱን ከትናንት በስትያ ምሽት ላይ መቆጣጠር እንደተቻለ የነገሩን የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ኤፍሬም ወንድዬ ናቸው።

 

በፓርኩ ውስጥ ባለው ተቀጣጣይ ክምችት ተዳፍኖ የቀረ እሳት ካለ በሚል የአሰሳ ስራ እየተሰራ ይገኛልም ብለዋል።

ስለ እሳቱ መነሻ ምክንያት ለማወቅ ማጣራት እየተካሄደ ነው ያሉን አቶ ኤፍሬም ከዚሁ ጋር በተገናኘ ተጠረጥረው የተያዙ ሰዎች ግን እንዳሉ ነግረውናል፡፡

 

ፓርኩን ህብረተሰቡ በእኔነት ስሜት እንዲጠብቀው በማድረግ ዘላቂ የሆነ የእሳት መከላከል ስራ እንሰራለን የሚሉት ሃላፊው፤ ጥያቄ እያስነሱብን ላሉ የዝግጅት ስራዎችም ምላሽ መስጠት እንዳለብን ተረድተናል ብለዋል።

 

የሰሜን ተራሮች ብሄራዊ ፓርክ 412 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ስፋት ያለው ሲሆን እንደ ዋልያ፣ ቀይ ቀበሮ እና ጭላዳ ዝንጀሮ ያሉ ብርቅዬ የዱር እንስሳት መገኛ መሆኑ ተነግሯል።

 

ንጋቱ ረጋሣ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

 

Telegram:  @ShegerFMRadio102_1

 

 

 

 

 

Recent Posts

See All
የሐምሌ 24 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ኮንጎ በኮንጎ ኪንሻሣ በኢቦላ የሚያዙ ሕሙማንና ወረርሽኙ የሚገድላቸው ሰዎች ብዛት በጣሙን እየጨመረ ነው ተባለ፡፡ በበሽታው መያዛቸው የተረጋገጠው ሰዎች ብዛት ከ3 ሺህ 400 መብለጡን አናዶሉ ፅፏል፡፡ ወረርሽኙ የገደላቸው ሰዎች ብዛት ከ1 ሺህ 500 በላይ መድረሱ ተነግሯል፡፡ በአገሪቱ በኢቦላ በሽታ የሚያዙ ሰዎች

 
 
 

1 Comment


Suman Sharma
Suman Sharma
Nov 05, 2025

If you arouse sexual passion in the hills, then our Call Girls in Manali are the best matches for you. Besides, they are competent to offer sensual GFE, classy companionship, and giving you a feeling of total relaxation and pleasure while on your trip. If you happen to be a solo traveler and want some private fun, then these gorgeous beauties are the ones who really understand how to delight you.

Like
Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page