top of page

መጋቢት 26፣2016 - ኢትዮጵያ የህዝቧን ቁጥር ሊስተካከል የተቃረበ ያህል በግ እና ፍየል እንዳላት ይነገራል

  • Apr 4, 2024
  • 1 min read

ኢትዮጵያ የህዝቧን ቁጥር ሊስተካከል የተቃረበ ያህል በግ እና ፍየል እንዳላት ይነገራል፡፡


ሀገሪቱ 90 ሚሊዮን በግ እና ፍየል እንዳላት ሲነገር ቢሰማም ለአብዛኛው ሰው ግን ስጋ ለዓመት በዓልም ቢሆን ብርቁ ነው፡፡


ዋጋውም የሚቀመስ አልሆነም፡፡


የኢትዮጵያ በግ እና ፍየሎች በየድንበሩ እየተነዱ የኮንትሮባንድ ሲሳይ መሆናቸውም አልቀረም፡፡


የበግ እና ፍየል ስጋ ብርቅ እንዳይሆን በማሰብ የተለያዩ ሀገር ዝርያዎችን ወደ ሀገር ቤት በማምጣት፣ ለማዳቀል የተደረገው ጥረትም እንደታሰበው አልሆነም፡፡


የበግ እና ፍየል ስጋ ብርቅ እንዳይሆን፣ ተሽጠውም ዶላር እንዳያመጡ፣ እርባታውም አካባቢን እንዳይጎዳ ለማድረግ ያለመ ፕሮጀክት ባለፉት 15 ዓመታት ሲሞከር መቆየቱን ሰምተናል፡፡


ፕሮግራሙ ''ማህበረሰብ አቀፍ የዝርያ ማሻሻያ'' እንደሚባል ሰምተናል፡፡


ከሌላ ሀገር ዝርያ ማምጣት ሳያስፈልግ እዚሁ ሀገር ቤት ካሉት የተሻሉትን ዝርያዎች በማዳቀል የሚሰራ ፕሮጀክት መሆኑን ተነግሯል፡፡


ፕሮጄክቱ በ 200 መንደሮች ተግባራዊ ተደርጎ ውጤቱም ጥሩ መሆኑን በአለም አቀፉ ድርቃማ አካባቢዎች የግብርና ምርምር (Icarda) ውስጥ የሚሰሩ ተመራማሪዎች ለሸገር ተናግረዋል፡፡


ንጋቱ ሙሉ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…





ShegerFM: @ShegerFMRadio102_1


Recent Posts

See All
የቱሪዝም ተጓዥችና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የሀገርን ገፅታ በመገንባትና ቱሪዝምን ለማስተዋወቅ ከፍተኛ አስተዋጾ እንዳላቸው ይነገራል፡፡

ነሐሴ 8 2018 የቱሪዝም ተጓዥችና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የሀገርን ገፅታ በመገንባትና ቱሪዝምን ለማስተዋወቅ ከፍተኛ አስተዋጾ እንዳላቸው ይነገራል፡፡ ኢትዮጵያም ይህንን መልካም አጋጣሚ በአግባቡ ለመጠቀም እነዚህ የዘርፉ ባለሙያዎች ወደ ሀገር ውስጥ ሲገቡ አስፈላጊውን መረጃና ጥበቃ ማድረግ እንደሚገባ ባለ

 
 
 
በአዲስ አበባ አጀንዳ ላይ የመከረውን ተመካካሪ ቡድን ጨምሮ ስምንቱም በአምስት መቶ ተሳታፊዎች የተቋቋሙ ቡድኖች በየቡድናቸው ሲመካከሩ ቆይተው በምክረ ሐሳቦች ላይ መስማማታቸውን ኮሚሽኑ ተናገረ።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ አጀንዳ ላይ የመከረውን ተመካካሪ ቡድን ጨምሮ ስምንቱም በአምስት መቶ ተሳታፊዎች የተቋቋሙ ቡድኖች በየቡድናቸው ሲመካከሩ ቆይተው በምክረ ሐሳቦች ላይ መስማማታቸውን ኮሚሽኑ ተናገረ። የምክክር ሂደቱን አስመልክተው ዛሬ ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት ምክትል ኮሚሽነር ሂሩት ገብረስላሴ፣ ሁሉም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page