top of page

ገዳ ባንክ አዲስ የሚያስገነባውን የህንፃ ዲዛይን ይፋ አደረገ፡፡

  • 5 hours ago
  • 1 min read

ነሐሴ 8 2018


ገዳ ባንክ አዲስ የሚያስገነባውን የህንፃ ዲዛይን ይፋ አደረገ፡፡



ባንኩ አስገነባዋለሁ ያለው ዋና መስሪያ ቤት ሜክሲኮ አካባቢ በ6 ሺህ 579 ካሬ ሜትር ላይ እንደሚያርፍም ተናግሯል፡፡


ገዳ ባንኩ ይፋ ያደረገው የህንፃው ዲዛይን የኪነ-ሕንፃ ጥበብን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር ያቀናጀ መሆኑን የተናገሩት የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ወልዴ ቡልቶ የዋና መሥሪያ ቤት ግንባታ ለማካሄድ የዲዛይን ውድድር ሲያካሂድ ቆይቷል ብለዋል።


ውድድሩ በዘርፉ በታወቁ ገለልተኛ ዳኞች ጥብቅ ምዘና ሲደረግበት የቆየ መሆኑ የተነገረ ሲሆን መስፈርቱን አሟልተው ለውድድር ከቀረቡ 18 ተወዳዳሪዎች አንድ ድርጅት አሸንፏል ተብሏል።


ወደ ስራ ከገባ ሶስት አመታትን ያስቆጠረው ገዳ ባንክ ከ32 ሺህ በላይ ባለአክሲዮኖች እንዳሉት ያነሳ ሲሆን ጠቅላላ ሀብቴ 12.6 ቢሊየን ብር ማደግ ችሏል ብሏል።


በተጨማሪም እስካሁን ከ110 በላይ ቅርንጫፎችን መክፈቱን የተናገረ ሲሆን በተጠናቀቀው በጀት አመትም ከ1 ቢሊየን ብር በላይ ትርፍ ማግኘቱን ባንኩ አስረድቷል።


ማርታ በቀለ

Recent Posts

See All
የነሐሴ 8 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#የተባበሩት_አረብ_ኢሚሬትስ የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ በሆርሙዝ ወሽመጥ በሁለት መርከቦቼ ላይ ጥቃት ሰንዝራለች ያለቻትን ኢራንን በብርቱ ኮነነቻት ተባለ፡፡ ኢራን በነዳጅ ጫኝ መርከቦቻችን ላይ ጥቃት ሰንዝራለች ሲል ከበድ ያለ ተቃውሞውን ያሰማው የኢሚሬትስ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት እንደሆነ አልጀዚራ እና AFP ፅፈዋ

 
 
 
የቱሪዝም ተጓዥችና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የሀገርን ገፅታ በመገንባትና ቱሪዝምን ለማስተዋወቅ ከፍተኛ አስተዋጾ እንዳላቸው ይነገራል፡፡

ነሐሴ 8 2018 የቱሪዝም ተጓዥችና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የሀገርን ገፅታ በመገንባትና ቱሪዝምን ለማስተዋወቅ ከፍተኛ አስተዋጾ እንዳላቸው ይነገራል፡፡ ኢትዮጵያም ይህንን መልካም አጋጣሚ በአግባቡ ለመጠቀም እነዚህ የዘርፉ ባለሙያዎች ወደ ሀገር ውስጥ ሲገቡ አስፈላጊውን መረጃና ጥበቃ ማድረግ እንደሚገባ ባለ

 
 
 
በአዲስ አበባ አጀንዳ ላይ የመከረውን ተመካካሪ ቡድን ጨምሮ ስምንቱም በአምስት መቶ ተሳታፊዎች የተቋቋሙ ቡድኖች በየቡድናቸው ሲመካከሩ ቆይተው በምክረ ሐሳቦች ላይ መስማማታቸውን ኮሚሽኑ ተናገረ።

ነሐሴ 7 2018 በአዲስ አበባ አጀንዳ ላይ የመከረውን ተመካካሪ ቡድን ጨምሮ ስምንቱም በአምስት መቶ ተሳታፊዎች የተቋቋሙ ቡድኖች በየቡድናቸው ሲመካከሩ ቆይተው በምክረ ሐሳቦች ላይ መስማማታቸውን ኮሚሽኑ ተናገረ። የምክክር ሂደቱን አስመልክተው ዛሬ ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡት ምክትል ኮሚሽነር ሂሩት ገብረስላሴ፣ ሁሉም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page