የቱሪዝም ተጓዥችና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የሀገርን ገፅታ በመገንባትና ቱሪዝምን ለማስተዋወቅ ከፍተኛ አስተዋጾ እንዳላቸው ይነገራል፡፡
- 3 hours ago
- 1 min read
ነሐሴ 8 2018
የቱሪዝም ተጓዥችና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች የሀገርን ገፅታ በመገንባትና ቱሪዝምን ለማስተዋወቅ ከፍተኛ አስተዋጾ እንዳላቸው ይነገራል፡፡
ኢትዮጵያም ይህንን መልካም አጋጣሚ በአግባቡ ለመጠቀም እነዚህ የዘርፉ ባለሙያዎች ወደ ሀገር ውስጥ ሲገቡ አስፈላጊውን መረጃና ጥበቃ ማድረግ እንደሚገባ ባለሙያዎች አሳስበዋል።
የቱሪዝም ተጓዥ ብሎገሮች ወይም ፀሀፊዎች በየሄዱበት የተመለከቱትን በጎም ይሁን መጥፎ ኩነቶች ቀጥታ ለተከታዮቻቸው ያሳውቃሉ፡፡
ይሄ ስራቸው ደግሞ በአለም አቀፍ አስጎብኚ ድርጅቶች ትልቅ ትኩረት እንደሚሰጠው ያነጋገርናቸው የቱሪዝም ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡
እንደ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ገንዘብ ከፍሎ በአለም አቀፍ የቱሪዝም ማስታወቂያ መስክ ላይ ማስተዋወቅ ለማይችሉ ሀገራት እነዚህ የቱሪዝም ፀሀፊዎች ፣ የማህበራዊ ትስስር ገፅ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ትልቅ የማስተዋወቅ ስራ በራሳቸው ፈቃድ እንደሚሰሩ ያስረዳሉ፡፡
ተጓዥ ፀሀፊያኑ ያዩትን ሁሉ በቀጥታ እንደወረደ ስለሚከትቡ በሌላ ጎን አደጋ እንዳለውም ይነገራል፡፡
ታዲያ ይህን እንዴት ነው እንደ ሀገር መጠቀም የሚቻለው ምንስ መሰራት አለበት ?
የዘርፉ ባለሙያዎችን ጠይቀናል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ.....
በረከት አካሉ
_edited.jpg)


Comments