top of page

መጋቢት 19፣2016 - ኤም ፔሳ ሳፋሪኮም የደንበኞቹ ብዛት 4.2 ሚሊዮን መድረሱን ተናገረ

  • sheger1021fm
  • Mar 28, 2024
  • 1 min read

የፋይናንስ አገልግሎት አቅራቢው ኤም ፔሳ ሳፋሪኮም የደንበኞቹ ብዛት 4.2 ሚሊዮን መድረሱን ተናገረ።


ኤም ፔሳ ሳፋሪኮም አዲስ ተጠቃሚ እና ግብይታቸውን በፔሳ ሳፋሪኮም ያካሄዱ ከ1 ሚሊዮን በላይ ደንበኞችን፣ ወኪሎችን እና ነጋዴዎችን የሸለመበት መርሃ ግብሩን በዛሬው እለት ተጠናቋል።

የሽልማት መርሀ ግብሩ ''ተረክ በ ኤም ፔሳ’’በሚል ባለፊት ሶስት ወራት የቆየ ነው ተብሏል።


በመርሃ ግብሩ አጠቃላይ ለእድለኞች የተሸለሙ 4 ዘመናዊ የቤት አውቶሞቢሎች፣ 24 ባጃጆች፣ 2160 ስልኮች እና በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዋጋ ያላቸው የአየር ሰዓት ሽልማቶችም በስድስት ዙር ለባለእድለኞች ተሸልመዋል።

የሽልማት መርሀ ግብሩ መጨረሻ የሆነው የስድስተኛው ዙር ሽልማት አሰጣጥ እና የመርኃ ግብሩ መዝጊያ ስነ ስርዓት ዛሬ በጊዮን ሆቴል ተካሂዷል።


ree

የመርሀ ግብሩ መጨረሻ በሆነው ስድስተኛ ዙር እድለኞች ከሁለት መኪኖች በተጨማሪ ሦስት ባጃጆች፣ 360 ስልኮች እና በሺህዎች የሚቆጠሩ የአየር ሰዓት እጣዎችን ተሸልመዋል።


የM-PESA ሳፋሪኮም የዲጂታል ፋይናንስ አገልግሎት ስትራቴጂክ አጋርነት ክፍል ኃላፊ የሆኑት አቶ ክፍሌ ኃ/እየሱስ መርሐ ግብሩ የእድለኞችን ሕይወት ከመለወጡ በተጨማሪ የገንዘብ ክፍያን እና ዝውውርን ያቀለለ፣ የM-PESA መተግበሪያን ያስተዋወቀ እና የብራንዱን ታዋቂነት ከፍ ያደረገ መርኃ ግብር ነበር ብለዋል።


ተረክ ኤም ፔሳ፤ ደንበኞች ስለ ዲጂታል የፋይናንስ አገልግሎት የተሻለ ግንዛቤ ለመፍጠር እና አጠቃቀሙን ለማጎልበት ያለመ መርሀ ግብር ነው ተብሏል፡፡


ኤም ፔሳ ሳፋሪኮም ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በገኘው የፋይናንስ አገልግሎት አቅራቢነት ፍቃድ በነሐሴ ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎች ማቅረብ ላይ መሆኑን ተናግሯል።



ንጋቱ ሙሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Recent Posts

See All
በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡

ታህሳስ 6 2018 በደብረ ብርሃን መጠለያ ጣቢያ ወደ ቀድሞ ቄያቸው ምስራቅ ወለጋ ጉብሰዮ ወረዳ የተመለሱ ከ141 በላይ አባዎራዎች ድጋፍ ስለተቋረጠባቸው መቸገራቸውን ተናገሩ፡፡ የአካባቢው ቡሣ ጎኖፋ ወይም የእርዳታ ማስተባበሪያ በበኩሉ ድጋፍ እንዲቀጥል ለሚመለከተው የበላይ አካል ባሳውቅም ድጋፍ ግን ሊቀጥል አልቻለም

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page