top of page

መጋቢት 17/2018 - የኔዘርላንድ ኢንስቲትዩት ፎር መልቲ ፓርቲ በመጪው ምርጫ የሚሳተፉ 80 ሴት እጩዎችን በመያዝ ውይይት ማድረጉ ተሰማ፡፡

  • 2 hours ago
  • 1 min read

መጋቢት 17/2018


የተለያዩ ሀሳቦችን በመያዝ በፖለቲካ ውስጥ የሚሳተፉ ሰዎች ከእርስ በእርስ ጥላቻ እና ካልተገባ መጠላለፍ ወጥተው በጋራ እንዲነጋገሩ እና በሀሳብ የበላይነት እንዲያምኑ እየሰራሁ ነው ያለው የኔዘርላንድ ኢንስቲትዩት ፎር መልቲ ፓርቲ በመጪው ምርጫ የሚሳተፉ 80 ሴት እጩዎችን በመያዝ ውይይት ማድረጉ ተሰማ፡፡


የኢትዮጵያ ባለዕራይ መሪዎች ማህበር ስራ አስፈፃሚ አካል ወ/ሪት ትዕግስት ወርቅነህ ፍፁም የተለያዩ አመለካከቶች እና የፓርቲ አቋም የያዙ ሰዎች በጋራ ሆነው ንግግር እንዲያደርጉ አካዳሚው እየሰራ ነው ሲሉ ለሸገር ነግረዋል፡፡


በተለያዩ ወቅቶች በዴሞክራሲ አካዳሚው ስልጠና መሰጠቱን የተናገሩት ወ/ት ትዕግስት ወጣት ሴቶች ለስልጠና የሚመጡት በአብዛኛው ከፖለቲካ ፓርቲ በመወከል ነው ይላሉ፡፡


አክቲቪስቶችም በስልጠናው ተሳትፈዋል ተብሏል፡፡


ፌዴራሊዝም ምንድነው ነው? ፖለቲካ ምንድነው? የሚሉ ሀሳቦችን ጨምሮ ሰልጣኞቹ አብረው በሚቆዩባቸው 21 ቀናት እና አንዱ የሌላውን ሀሳብ እንዲረዳና መግባባት እንዲፈጥሩ በጋራ የሚሰሯቸውን ስራዎች ይጭራልም ሲሉ ወ/ት ትዕግስት ነግረውናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….

የኔነህ ሲሳይ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page