top of page

ጋዜጠኞች ያላግባብ መታፈንና እስርን የመሰለ የሰብአዊ መብት ጥሰት ሲደርስባቸውም በፍርድ ቤት ጭምር ክርክር የሚያደርግ ድርጅት ስራ ጀምሯል፡፡

  • 1 hour ago
  • 1 min read

መጋቢት 17/2018


ጋዜጠኞች ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲሰሩ ፣ የሚድያ ምህዳሩ እንዲሰፋ ፣ ጋዜጠኞች ያላግባብ መታፈንና እስርን የመሰለ የሰብአዊ መብት ጥሰት ሲደርስባቸውም በፍርድ ቤት ጭምር ክርክር የሚያደርግ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት በይፋ ስራ ጀምሯል፡፡


በሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ባለስልጣን ተመዝግቦ በይፋ ትናንት ስራ ጀምሯል የተባለው ሎውየርስ ፎረ ሚዲያ (Lawyers for media) የተሰኘ ስያሜ የተሰጠው ተቋም ነው፡፡


በዩኔስኮ እገዛ በፕሮጀክት ደረጃ የጀመርናቸው ስራዎች ራሱን ችሎ በተቋም ደረጃ በስፋት እየሰራ ይቀጥላል ያሉን የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ድርጅቶች ህብረት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት አቶ መሱድ ገበየሁ ናቸው፡፡



በሁሉም ክልሎች የሚሰሩ የህግ ባለሙያዎች የተካተቱበት ለሚድያው ዘርፍ መጠናከርና የሚያስፈልገው የህግ ድጋፍ የሚሰጥ መሰል ማህበር ማቋቋም ያስፈለገበት ምክንያትም የሚድያ ምህዳሩ እየሰፋ እንዲሄድ ለማገዝ ነው ብለዋል፡፡


ከዚህ ባሻገር ጋዜጠኞች ያላግባብ የመታፈንና የመታሰር ችግረ ሲደርስባቸው የህግ ምክር መስጠትና በፍርድ ቤትም ነጻ ጥብቅና እንዲያገኙ ማስቻል ተቋሙ ከሚከውናቸው ስራዎች መካከል ይሆናል ተብሏል፡፡


ከእስር ከተፈቱ በኋላም ቢሆን የስነ ልቦና ድጋፍ እንዲያገኙና ሀላፊነታቸው መወጣታቸውን እንዲቀጥሉ ማገዝ የ*Lawyers for media* ሀላፊነት ነው ብለዋል ዋና ዳይክተሩ አቶ መስኡድ፡፡


ተቋሙ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ እና መረጃ የማግኘት ፣ መብቶች በህጉ መሰረት እንዲከበሩ ፣ የጋዜጠኞች የመገናኛ ብዙሃን ደህንነት ተጠብቆ እንዲሰሩ ለማስቻል ይሰራል ተብሏል፡፡


ተቋሙ በህግ እውቅና አግኝቶ ራሱን ችሎ እንዲሰራ ያስፈለገው የሚድያ ምህዳሩ እየጠበበ መምጣቱ በተለያየ መንገድ የሚታይ በመሆኑና ይህን ችግር ማሻሻል አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ መሆኑንም ሰምተናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….


ትዕግስት ዘሪሁን


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page