በአዲስ አበባ መንገዶች ከተሰሩበት አላማ ውጪ እየዋሉ መሆኑን የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ተናገረ፡፡
- 17 minutes ago
- 1 min read
መጋቢት 17/2018
በአዲስ አበባ መንገዶች ከተሰሩበት አላማ ውጪ እየዋሉ መሆኑን የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ተናገረ፡፡
ባለስልጣኑ እንዳለው በኮሪደር ልማቱ ስራ የመኪና ማቆሚያዎች በተለያዩ ስፍራዎች ተገንብተዋል ያለ ሲሆን በከተማው መውጪያ እና መግቢያ አካባቢ ትላልቅ መኪኖች እቃ ጭነው ለረጅም ሰዓት ሲቆሙ እየተመለከትሁኝ ነው ብሏል፡፡
የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ እያሱ ሰለሞን ባለፉት 8 ወራት ውስጥ 111 ኪሎ ሜትር የአስፓልት መንገድ ጥገና መከናወኑን ነግረውናል፡፡

ክረምት እየመጣ መሆኑን ተከትሎ የጎርፍ ስጋ ባለባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ድልድዮች፣ የፍሳሽ ማስወገጃ ቱቦዎች ጥገና እየተከናወነ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
አዲስ አበባ ወስጥ መንገዶች በየጊዜው ነው እድሳት የሚደረግላቸው ምክንያቱ ደግሞ ህብረተሰቡ የኔነት ስሜት ኖሮት መንገዶችን እየጠበቃቸው ባለመሆኑ ነው ብለዋል፡፡
በተያዘው አመት ለመንገድ አዲስ ግንባታ እና ጥገና አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ያዘው በጀት 31 ቢሊዮን ብር መሆኑን ሰምተናል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….
ወንድሙ ሀይሉ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://shorturl.at/18TS1
Telegram : https://shorturl.at/68aeK
Facebook፡ https://shorturl.at/tm5Q4
WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx
X :- https://x.com/shegerfm?s=2
LinkedIn: https://shorturl.at/Vfe6i
Tiktok : https://shorturl.at/lhYiv
Instagram: https://shorturl.at/9X4S7





Comments