top of page

በአንድ ይዞታ ላይ ሁለት እና ሶስት ካርታ ወይም የይዞታ ማረጋገጫ ለምን ሊወጣ ይችላል?

  • 1 hour ago
  • 1 min read

መጋቢት 17/2018


በአዲስ አበባ ከመሬትና መሬት ነክ ጉዳዮች ጋር በተገናኘ ዛሬም አሁንም ከፍተኛ ቅሬታና የአፈፃፀም ችግር እንዳለ ይሰማል።


ከተማ አስተዳደሩ በተለያየ ዙር በሊዝ የጨረታ ቦታዎችን እያወዳደረ ለባለሀብቶች እያስተላለፈ ነው።


የተወሰኑ የልማት ተነሺዎችም ሆኑ በጨረታ ከከተማ አስተዳደሩ አሸንፈው የወሰዱ ፤ ቦታ ለማግኘት ከማእከል ከጨረሱ በኋላ የተሰጣቸውን ቦታ ለመቀበል እንደተቸገሩ ሰምተናል።


የዚህ ዋነኛ ችግር ደግሞ በተለይ የአርሶ አደር ቦታ ነው ፤ ካሳ አልተሰጠንም አልተወሰደም እና ሌሎች ምክንያቶችም ለከተማ አስተዳደሩ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ራስ ምታት እንደሆነበት ሰምተናል።


ለመሆኑ የፕላን ተቃርኖ ያለበት ወይም ለአረንጓዴ ስፍራ ቦታ የተያዘ ቦታ የሆነ አገልግሎት ግንባታ የተፈጸመበት ቦታስ ሊስተካከልና አገልግሎቱ ሊስማማ የሚችለው እንዴት ነው?


መሬትን የሚያስተዳድረው መንግስት ሆኖ ሳለ ፤ የካርታ መደራረብ አለ፤ በአንድ ይዞታ ላይ ሁለት እና ሶስት ካርታ ወይም የይዞታ ማረጋገጫ ለምን ሊወጣ ይችላል?


በዚህ ጉዳይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ሀላፊውን አቶ መኮንን ያኢን ጠይቀናል።


ሃላፊው አቶ መኮንን በአዲስ አበባ ከመሬት ጋር የሚገናኙ ችግሮች አሁንም አሉ ግን እየተፈቱ ነው ይላሉ፡፡


ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ….


ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


YouTube : https://shorturl.at/18TS1

WhatsApp : https://shorturl.at/8vwRx

X :- https://x.com/shegerfm?s=2

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page