top of page

መስከረም 30፣2017 - በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መንግስታት መካከል ያለው ግንኙነት እንደቀድሞ በሰላማዊ ትብብርና ግንኙነት መንፈስ እንደቀጠለ ነው ምንም አዲስ ነገር የለም ተባለ

  • Oct 10, 2024
  • 1 min read

በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መንግስታት መካከል ያለው ግንኙነት እንደቀድሞ በሰላማዊ ትብብርና ግንኙነት መንፈስ እንደቀጠለ ነው ምንም አዲስ ነገር የለም ተባለ፡፡


የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ፅ/ቤት ሀላፊ አምባሳደር ነቢያት በወቅታዊ ጉዳይ ዙሪያ በሰጡት መግለጫቸው ስለ ኢትዮ ኤርትራ ወቅታዊ ግንኙነት ተጠይቀው በሰጡት ምላሽ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለው ግንኙነት እንደ በፊቱ ቀጥሏል ምንም የተለወጠ ነገር የለም ሲሉ መልሰዋል፡፡


ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት በሰብአዊ መብቶች ካውንስል አባል እንድትሆን ለሶስተኛው ጊዜ መመረጧንም አምባሳደር ነቢያት ተናግረዋል፡፡


በሊባኖስ የሚገኙ ዜጎችን በሚመለከት በሰጡት ማብራሪያ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በቤይሩት በችግር ውስጥ ያሉ ሁሉንም ዜጎችን የማስወጣት ስራ ለመስራት የመኖሪያ ፈቃድ ያለውና የሌለው ብሎ ሳይለይ ወደ ሀገር ለመመለስ የፈቀዱ ኢትዮጵያዊንን እየመዘገበ ነው፡፡


ይሁንና ከዛሬ ነገ በሊባኖስ ያለው ሁኔታ ይሻሻላል በሚል የሚመዘገበው ዜጋ እያመነታ በመሆኑ በበቂ መጠን ምዝገባ እየተካሄደ አለመሆኑን ጠቅሰዋል፡፡


ዜጎች ወደ ሀገር ለመመለስ ምዝገባ ሲደረግ ገንዘብ እንዲከፍሉ እየተጠየቁ ነው ይህ ለምን ሆነ ተብለው የተጠየቁት አምባሳደር ነቢያት፤ እስከሚያውቁት ድረስ ምንም ዓይነት የገንዘብ ክፍያ እንዳልተጠየቀ ይሁንና የነገሩን እውነት ለማጣራት የበለጠ መረጃ መሰብሰብ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡


የኔነህ ሲሳይ


Recent Posts

See All
በኢትዮጵያ እያንዳንዱ ብሄረሰብ የራሱን ታሪክ ብቻ ለይቶና አጉልቶ የሚያቀርብበት ስርዐት መቀየር እንዳለበት የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ተናገሩ ።

ሐምሌ 23 2018 በኢትዮጵያ እያንዳንዱ ብሄረሰብ የራሱን ታሪክ ብቻ ለይቶና አጉልቶ የሚያቀርብበት ስርዐት መቀየር እንዳለበት የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ ተናገሩ ። በኢትዮጵያ የብሄረሰቦች ታሪክ ጥልቅ ትስስር እና መስተጋብር ያለው ነው ብለዋል። የኢትዮጵያ የታሪክ ባለሞያዎች ማህበር ከላይፍ ኤንድ ፒስ ኢንስ

 
 
 
በ2018 በጀት ዓመት ከ1.2 ቢሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል።

ሐምሌ 23 2018 በ2018 በጀት ዓመት ከ1.2 ቢሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን የግብርና ሚኒስቴር መረጃ ያሳያል። በየዓመቱ በሀገሪቱ የሚገኘው የምርት መጠን እያደገ እንደሚመጣ ሪፖርቶች ያመልክታሉ። በገበያው ውስጥ ግን የምርት ዋጋ ከአመት አመት እየጨመረ እንጂ ሲቀንስም አይታይም። ይህ ለምን ሆነ? እውነትስ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page