top of page

መስከረም 29 2018 - በአፍሪካ የንግድ ቀጠና ስምምነት መግባት ለሀገር ውስጥ ነጋዴ፣ ለሸማቹ እና በአጠቃላይ በንግድ ስርዓቱ ውስጥ ይዞ የሚመጣው እድልና ተፅእኖ ምንድን ነው?

  • sheger1021fm
  • Oct 9
  • 1 min read

የስጋ፣ አትክልትና ፍራፍሬ ምርቶችን በመላክ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠናውን እንደምትቀላቀል ተነግሯል።


ለመሆኑ ወደዚህ ንግድ መግባቱ ለሀገር ውስጥ ነጋዴ፣ ለሸማቹ እና በአጠቃላይ በንግድ ስርዓቱ ውስጥ ይዞ የሚመጣው እድልና ተፅእኖ ምንድን ነው?


በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የምግብና ሥነ-ምግብ ትምህርት ክፍል ተባባሪ ፕሮፌሰር እና የኢትዮጵያ የሸማቾች ጥበቃ ድርጅት የቦርድ አባል የሆኑት አሻግሬ ዘውዱ(ዶ/ር)፤ ይህ ሂደት ለሀገር ውስጥ ሸማች ምርትን በአማራጭ፣ በጥራትና በተሻለ ዋጋ እንዲያገኝ የሚያደርገው ነው ብለዋል።


የተለያዩ ሀገሮች ምርታቸውን ከቀረጥ ነፃ ስለሚያስገቡ ሸማቹ ተጠቃሚ መሆኑ ጥርጥር የለውም ብለዋል።


ወደ ሌሎቹ ሀገሮች ኢትዮጵያ ምርቷን በብዛት ለመላክና ለመወዳደር ግን በጥራት እና በሌላውም መመዘኛ በደንብ መስራትን የሚጠይቅ እንደሚሆን አንስተዋል።


የሀገር ውስጥ ነጋዴውም ለተወሰነ ጊዜ በዚህ ውስጥ የመዝለቅ ፈተና ሊገጥመው ይችላል ብለዋል።


በየጊዜው ውጤትና ችግሩን እየፈተሹ እያረሙ መሄድም እንደ ሀገር የሚጠበቅ ስራ መሆኑን አብራርተዋል።


ቴዎድሮስ ወርቁ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page