top of page

መስከረም 27 2018 - ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ እና ጎህ ቤቶች ባንክ በጋራ ሆነው በአይነቱ አዲስ ነው ያሉትን የቤት ግንባታ ፕሮጀክት ዛሬ ይፋ አድርገዋል።

  • sheger1021fm
  • Oct 7
  • 1 min read

ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ እና ጎህ ቤቶች ባንክ በጋራ ሆነው በአይነቱ አዲስ ነው ያሉትን የቤት ግንባታ ፕሮጀክት ዛሬ ይፋ አድርገዋል።


አሰራሩም በቅድሚያ አንድ ቤት ፈላጊ ወደ ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ በመሄድ የሚፈልውን አይነት ቤት መርጦ ፎርም ይሞላል፡፡


ቀጥሎም ወደ በጎህ ቤቶች ባንክ በመሄድ በግሉ አካውንት ከፍቶ ተቀማጭ 500,000 ብር መክፈልና በየወሩ መቆጠብ አለበት ተብሏል፡፡


በዚህ ሂደት ውስጥ ገንዘቡ በራሱ በግለሰቡ አካውንት የሚቀመጥ እንጂ ወደ ኮምፓስም ሆነ ወደ ጎህ አካውንት የሚገባ ምንም አይነት ገንዘብ አይኖርም ብለዋል።


ቤት ፈላጊው የቆጠበው ገንዘብ ከግል አካውንቱ ወጥቶ ወደ ቤት ገንቢው ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ የሚተላለፈው ቤቱ ተጠናቅቆለት ካርታ ሲረከብ ብቻ መሆኑን ሰምተናል፡


ቆጣቢው 15 በመቶ ወለድ ይታሰብለታል፣ በሂደት ይቅርብኝ ብሎ የቆጠበውን ገንዘብ ማውጣት ከፈለገም ለባንኩ ቀድሞ በማሳወቅ ማዉጣት ይችላል ተብሏል፡፡


ደንበኛው ገንዘቤን ላውጣ በማለቱ ምንም አይነት የአገልግሎት ክፍያም ሆነ ቅጣት ክፍያ የለውም ሲሉ የኮምፓስ ፕሮፐርቲስ እና ጎህ ቤቶች ባንክ ሀላፊዎች አስረድተዋል፡፡


የባንክ እገዛ የሚፈልግ ደንበኛም ቀሪ ክፍያውን ከባንክ ጋር በማያያዝ ቤቱን መረከብ እንደሚችል ተጠቅሷል፡፡


አሰራሩ ከተማው ላይ ከሪል ስቴት ጋር ተያይዞ በተደጋጋሚ የሚሰማውን ቅሬታ እና ችግር በእጅጉ ይቀርፈዋል የሚል እምነት እንዳላቸውም ኮምፓስ ፕሮፐርቲስ እና ጎህ ቤቶች ባንክ ጠቁመዋል።


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Recent Posts

See All
ጥቅምት 20 2018 - የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ

የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳቦች ያለ በቂ ምክንያት የማይፈፅሙ ተቋማት በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ቢሞክርም ባለው የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡ ተቋሙ የአስተዳደር በደል ደረሰብን እምባችን ይታበስልን የሚሉ አቤት ባዮችን ቅሬታ በመቀበል

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page