top of page

መስከረም 27 2018 - ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ስምምነትን ማጠናቀቋን ተከትሎ በሸቀጦች ንግድ ዘርፍ መስከረም 29/2018 በይፋ ትጀምራለች ተባለ

  • sheger1021fm
  • Oct 7
  • 1 min read

ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ ንግድ ስምምነትን ማጠናቀቋን ተከትሎ በሸቀጦች ንግድ ዘርፍ መስከረም 29/2018 በይፋ ትጀምራለች ተባለ፡፡


ይህንን ያሉት የንግድ ትስስርና ወጪ ንግድ ፕሮሞሽን ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታዋ ወ/ሮ ያስሚን ውሀብረቢ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ ነው፡፡


በዚህም የመጀመሪያው የንግድ ልውውጥ በምስራቅና በደቡብ አፍሪካ ሀገራት ላይ እንደሚደረግ ተነግሯል፡፡

ree

በማስጀመሪያ ንግዱ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ካርጎ፤ ሥጋ፣ አትክልትና ፍራፍሬ እንዲሁም በየብስ ትራንፖርት ቡና፣ የጥራጥሬ ምርቶችና የቅባት እህሎች ወደ ኬንያ፣ ሶማሊያ እና ወደ ደቡብ አፍሪካ ይላካል ብለዋል፡፡


አህጉራዊ ነፃ ንግድ ስምምነቱ ትግበራው ለኢትዮጵያ ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች ይኖሩታል ያሉት ሚኒስትር ዴኤታዋ ለኢትዮጵያ ንግድ ተወዳዳሪነትና ኢንቨስትመንትን ያነቃቃል፣ ሰፊ የሥራ ዕድል ይፈጥራል ሲሉ አስረድተዋል፡፡


ለሸማቹ ህብረተሰብ የተሻለ አማራጭ የምርት አቅርቦት ያስገኛል ብለዋል፡፡


የጉምሩክ ሂደቶችን ማዘመን እና የምርቶችን ጥራት መጠበቅ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል፡፡


ማርታ በቀለ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Recent Posts

See All
ጥቅምት 20 2018 - የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ

የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳቦች ያለ በቂ ምክንያት የማይፈፅሙ ተቋማት በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ቢሞክርም ባለው የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡ ተቋሙ የአስተዳደር በደል ደረሰብን እምባችን ይታበስልን የሚሉ አቤት ባዮችን ቅሬታ በመቀበል

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page