መስከረም 26 2018 - በተያዘው የበጀት ዓመት 9 በመቶ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት እድገትን የማሳካት ግብ መቀመጡ ተነገረ፡፡
- sheger1021fm
- Oct 6
- 1 min read
በተያዘው የበጀት ዓመት 9 በመቶ ጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት እድገትን የማሳካት ግብ መቀመጡ ተነገረ፡፡
በበጀት ዓመቱ #የዋጋ_ንረትን ወደ ነጠላ አሀዝ እንዲወርድ ይደረጋልም ተብሏል፡፡

በህዝብ እንደራሴዎችና የፌዴሬሽን ምክር ቤት መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት ፕሬዘዳንት ታዬ አፅቀስላሴ የኢትዮጵያ ግብርና በተፈጥሮ ላይ መሰረት ያደረገ፤ ፍላጎቱ ደግሞ በውጪ ምርቶች ላይ ጥገኛ የሆነ ነው ብለዋል፡፡
ይህም ኢትዮጵያን ለአለም አቀፍ ተለዋዋጭ ሁኔታ ተጋላጭ አድርጓታል ብለዋል፡፡
እነዚህን ፈተናዎች መቋቋም የሚችል መንገድን መከተል የግድ እንደሚልም አንስተዋል፡፡
ምርት እና ምርታማነትን ፣ በዓይነትም በመጠንም የማሳደግ ስራ በተያዘው የበጀት አመት ይሰራል ያሉት ፕሬዘዳንት ታዬ ይህንኑ በማድረግ የሀገር ውስጥ ምርት እድገትን ዘጠኝ በመቶ ማድረግ የዋጋ ግሽበቱንም ወደ ነጠላ አሀዝ ማውረድ የመንግስት ግብ ይሆናል ብለዋል፡፡
ቴዎድሮስ ወርቁ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s
👔LinkedIn ፡ https://tinyurl.com/tyfaekvx












Comments