top of page

መስከረም 23 2018 - ወጋገን ባንክ በስዊፍት የሚላክን ዓለም አቀፍ ክፍያ ወጋገን ሞባይል መተግበሪያን በመጠቀም በኦንላይን መከታተል የሚያስችላቸውን  አገልግሎት  መስጠት መጀመሩን ተናገረ

  • sheger1021fm
  • Oct 3
  • 1 min read

ወጋገን ባንክ በስዊፍት የሚላክን ዓለም አቀፍ ክፍያ ወጋገን ሞባይል መተግበሪያን በመጠቀም በኦንላይን መከታተል የሚያስችላቸውን  አገልግሎት  መስጠት መጀመሩን ተናገረ፡፡


አገልግሎቱ በተለይም በገቢ እና ወጪ ንግድ ዘርፍ የተሰማሩ ኮርፖሬት ደንበኞች ያገለግላል ተብሏል።

ree

ደንበኞች በስዊፍት ክፍያ ሲፈፅሙ የክፍያ ትዕዛዝ በባንኩ ከተሰጠበት ጊዜ ጀምሮ ገንዘቡ ለታለመበት ግለሰብ ወይም ተቋም እስከሚደርስ ድረስ ያለውን ሂደት በሚደርሳቸው ልዩ የመከታተያ ቁጥር አማካኝነት በመጠቀም በወጋገን ሞባይል መተግበሪያ በኩል በቀጥታ መከታተል እና ክፍያው መፈጸሙን ማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑ ተጠቅሷል፡፡


ወጋገን ባንክ የጀመረው የኦንላይን የስዊፍት ክፍያ መከታተያ ስርዓት ባንኩ ለደንበኞቹ ሲሰጥ የቆየውን ዓለም አቀፍ የክፍያ አገልግሎት ፈጣን፣ ግልፅነት የሰፈነበት፣ ደህንነቱ የተጠበቀ እና የበለጠ አስተማማኝ ያደርገዋል ሲል ባንኩ በላከልን መግለጫ አስረድቷል።


ደንበኞች ክፍያቸውን ወደ ባንኩ መምጣት ሳይጠበቅባቸው  በስልካቸው መከታተል የሚያስችል መሆኑም ተነግሯል፡፡


በተያያዘም አዲሱ የኦንላይን ክፍያ መከታተያ ስርዓት ዓለም አቀፍ ክፍያዎችን ለታለመለት ዓላማ እንዲደርሱ በማስቻል የሀገሪቱን ገቢ እና ወጪ ንግድ ለማቀላጠፍ እንዲሁም አዋጪ እንዲሆን በማገዝ በኩል የላቀ አስተዋፅኦ ያበረክታል ተብሎለታል።


አገልግሎቱን ለማግኘት ደንበኞች የወጋገን ሞባይል መተግበሪያ ስር ስዊፍት የሚለውን አማራጭበመከተል እና ልዩ የኦንላይን ክፍያ መከታተያ ኮድ ቁጥራቸውን  በማስገባት መጠቀም ይችላሉ  ተብሏል፡።


ንጋቱ ሙሉ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…


Recent Posts

See All
ጥቅምት 20 2018 - የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ

የሚሰጣቸውን ምክረ ሃሳቦች ያለ በቂ ምክንያት የማይፈፅሙ ተቋማት በህግ እንዲጠየቁ ለማድረግ ቢሞክርም ባለው የፍትህ ስርዓት ችግር ምክንያት ስራው ላይ እክል እየገጠመው መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብ እምባ ጠባቂ ተቋም ተናገረ፡፡ ተቋሙ የአስተዳደር በደል ደረሰብን እምባችን ይታበስልን የሚሉ አቤት ባዮችን ቅሬታ በመቀበል

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page