top of page

መስከረም 11፣2017 - የፀረ HIV መድሃኒት ተጠቃሚዎች እና የኤች አይቪ ኤድስ ቫይረስ ተጠቂዎች የሚያገኙትን አገልግሎት የተሻለ ለማድረግ ስምምነት ተደረገ

  • Sep 21, 2024
  • 1 min read

በኢትዮጵያ የፀረ ኤች አይቪ ኤድስ(HIV) መድሃኒት ተጠቃሚዎች እና የኤች አይቪ ኤድስ ቫይረስ ተጠቂዎች የሚያገኙትን አገልግሎት የተሻለ ለማድረግ ስምምነት ተደረገ፡፡


ስምምነቱን ያደረጉት የአሜሪካ ፕሬዝዳንት የአስቸኳይ ጊዜ የኤች አይቪ ኤድስ እርዳታ ፔፕፋር እና ጣምራ ለማህበራዊ ልማት ድርጅት ናቸው፡፡


በአሜሪካ የፕሬዝዳንቱ የአስቸኳይ ጊዜ የኤች አይቪ ኤድስ እርዳታ ፔፕፋር ባለፉት 20 ዓመታት ኢትዮጵያ ውስጥ ኤች አይቪ ኤድስን ለመከላከልና ተጠቂዎችን ለመርዳት የሚሆን 3 ቢሊዮን ዶላር እርዳታ አድርጌያለሁ ብሏል፡፡


በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ማሲንጋ ፔፕፋር ኮሚቲኒ ሊድ ሞኒተር ፕሮግራም በሚል እየከወነው ያለው ስራ እራሱ ማህበረሰቡ ተሳታፊ ያደረገ ነው፤ ምክንያቱ ደግሞ ቀጣይነት ያለው መሰረተ ልማት ለመገንባት ነው ብለዋል፡፡


የጣምራ ለማህበራዊ ልማት ድርጅት ዋና ዳይሬክተር አቶ ብሩክ ይርጋለም ኮሚኒቲ ሊድ ሞኒተር ፕሮግራም የፀረ ኤች አይቪ ኤድስ መድሀኒት ተጠቃሚ ሰዎች በጤና ተቋማት የሚያጋጥማቸው ችግሮችን ለመፍታት ይረዳል ብለዋል፡፡


ይህ ሲሆን የማህበረሰቡ እና እራሳቸው አገልግሎቱን የሚጠቀሙ ሰዎች ስለሚሳተፉ ውጤታማ እንዲሆን ያግዛል ሲሉ ነግረውናል፡፡


ሙሉ ዘገባውን በድምፅ ለማድመጥ ይህንን ይጫኑ…



በረከት አካሉ

Recent Posts

See All
የሐምሌ 23 2018 የውጪ ሀገር ወሬዎች

#ግብፅ በግብፅ የሜዴትራኒያን የባህር ዳርቻ የነበረ የአሜሪካ የጋዝ ማጠራቀሚያ መርከብ በድሮን ተመታ ተባለ፡፡ ሁለት የደህንነት ምንጮች መርከቡ በድሮን እንደተመታ አረጋግጠውልኛል ሲል ሬውተርስ ፅፏል፡፡ መርከቡ በድሮን እንደተመታ በእሳት መያያዙ ታውቋል፡፡ ቃጠሎው ወደ ሌላ መርከብም ተጋብቶ ነበር ተብሏል፡፡ ኋላ ግን

 
 
 
የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ማሳደግ፣አፍሪካዊያን የጋራ መጪ እድላቸውን እንዲቀርፁ ማገዝ ያስፈልጋል ተባለ።

ሐምሌ 23 2018 የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ማሳደግ፣አፍሪካዊያን የጋራ መጪ እድላቸውን እንዲቀርፁ ማገዝ ያስፈልጋል ተባለ። የአፍሪካ ሀገሮች እርስ በእርስ፣በአፍሪካና በሩሲያ እንዲሁም አፍሪካ ከተቀረው ዓለም ጋር ያላትን የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ማሳደግን ዓለማው ያደረገ ዓለም አቀፍ ጉባኤ በተባበሩት መንግስታት የአ

 
 
 

Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play
  • Facebook
  • X
  • Youtube
  • TikTok
  • Telegram
  • Whatsapp

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2026 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page