ሐምሌ 28 2017 - ኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር አክሲዮን ማህበር መሰረተ ልማቱ የተገነባበትን ከፍተኛ እዳ ለመክፈል የምችልበትን የ3 ዓመት ስትራቴጂ ነድፌአለሁ አለ
- sheger1021fm
- Aug 4
- 1 min read
የኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር አክሲዮን ማህበር መሰረተ ልማቱ የተገነባበትን ከፍተኛ እዳ ለመክፈል የምችልበትን፤ የ3 ዓመት ስትራቴጂ ነድፌአለሁ አለ፡፡
ምድር ባቡሩ በዘንድሮ የስራ ዘመንም 4.6 ሚሊዮን ቶን ገቢ ወጪ ጭነት ለማመላለስ ማቀዱን ሰምተናል።
በባለፈው የስራ ዘመን 2.6 ሚሊየን ቶን ጭነት ያመላለሰው ምድር ባቡሩ በ3 ዓመቱ ስትራቴጂ ዘንድሮ የጭነት መጠኑን እጥፍ በማድረግ እንደሚሰራ አስረድቷል።
ኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር በስስትራቴጂው የባቡር ፍጥነት መጨመር፣ የገቢ ወጪ ንግድ ማቀላጠፍ እና ከአለም ሀገሮች ወደ መሐል ሀገር ኢትዮዽያ ከፍተኛ ወጪ ገቢ ጭነት ለማመላለስ ወገቡን መታጠቁን ሰምተናል።
ምድር ባቡሩ በ3 ዓመቱ የፍጥነት ገደቡንም አሁን ካለበት በሰአት 60 ኪሎ ፍጥነቱን እንደሚጨምር ተናግሯል።
ሙሉ ዘገባውን ያዶምጡ....
ተህቦ ንጉሴ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
📌 Telegram; https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📌 YouTube: https://shorturl.at/P4mpX
📌 WhatsApp: https://tinyu.com/ycxjmm3s












Comments