top of page

ሐምሌ 28 2017 - ኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር አክሲዮን ማህበር መሰረተ ልማቱ የተገነባበትን ከፍተኛ እዳ ለመክፈል የምችልበትን የ3 ዓመት ስትራቴጂ ነድፌአለሁ አለ

  • sheger1021fm
  • Aug 4
  • 1 min read

የኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር አክሲዮን ማህበር መሰረተ ልማቱ የተገነባበትን ከፍተኛ እዳ ለመክፈል የምችልበትን፤ የ3 ዓመት ስትራቴጂ ነድፌአለሁ አለ፡፡


ምድር ባቡሩ በዘንድሮ የስራ ዘመንም 4.6 ሚሊዮን ቶን ገቢ ወጪ ጭነት ለማመላለስ ማቀዱን ሰምተናል።


በባለፈው የስራ ዘመን 2.6 ሚሊየን ቶን ጭነት ያመላለሰው ምድር ባቡሩ በ3 ዓመቱ ስትራቴጂ ዘንድሮ የጭነት መጠኑን እጥፍ በማድረግ እንደሚሰራ አስረድቷል።


ኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር በስስትራቴጂው የባቡር ፍጥነት መጨመር፣ የገቢ ወጪ ንግድ ማቀላጠፍ እና ከአለም ሀገሮች ወደ መሐል ሀገር ኢትዮዽያ ከፍተኛ ወጪ ገቢ ጭነት ለማመላለስ ወገቡን መታጠቁን ሰምተናል።


ምድር ባቡሩ በ3 ዓመቱ የፍጥነት ገደቡንም አሁን ካለበት በሰአት 60 ኪሎ ፍጥነቱን እንደሚጨምር ተናግሯል።


ሙሉ ዘገባውን ያዶምጡ....


ተህቦ ንጉሴ


የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…




Comments


Sheger App Logo
iOS Store
Google Play

    ሸገር
102.1

ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር! 

Sheger Radio | Sheger 102.1FM  © 2025 Adey Tensae Media & Entertainment PLC.  

bottom of page