ህግ አውጪ ተቋማት በጥናትና ምርምር ለመደገፍ ይሰራል የተባለለት ተቋም ስራ መጀመሩን ተነግሯል
- sheger1021fm
- 17 minutes ago
- 1 min read
ህዳር 4 2018
እንደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያሉ ህግ አውጪ ተቋማት በጥናትና ምርምር ለመደገፍ ይሰራል፣ ለሰላምና ዲሞክራሲ ግንባታ እገዛ ያደርጋል የተባለለት ተቋም ስራ መጀመሩን ተነግሯል፡፡
እንደራሴዎች በተገኙበት ስራ መጀመሩን የተናገረው ብሪጅ ሪሰርችና ኢኖቬሽን የተባለ ድርጅት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ 18 የህግ አውጪ ምክር ቤቶችን በገለልተኝነት ሙያዊ የሆነ የአቅም ግንባታ ስራዎችን እሰራለሁ ብሏል፡፡፡
ህግ አውጪዎች ያሉባቸው ክፍተቶች ምንድናቸው? የሚለውን በመለየት በጥናትና ምርምር ለማገዝ መቋቋሙን የነገሩን የድርጅቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ ቃለ አብ ታደሰ(ዶ/ር) ናቸው፡፡

ተቋሙ ወደ ስራ ከገባ የመጀመሪያ የሆነውን ጥናት ቢያደርግም ወደፊት ሌሎች ምርምርና ጥናት የሚደረግባቸው ስራዎችን ከምክር ቤቱ ጋር እንደሚያደርግም አስረድተዋል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ የሲቪክ ማህበራትና ምሁራን በዚህ በምክር ቤት ዙሪያ የሚደረግ ጥናትና ምርምርን ገሸሽ ያደረጉት ጉዳይ ነው የሚሉት ዋና ስራ አስፈፃሚው የመመረቂያ ጥናታዊ ጽሁፎችን ከማድረግ በዘለለ ክፍተቶችን ሲሞሉ አይታዩም ብለዋል፡፡

የምክር ቤት አባሉ አቶ ፍሬው ተስፋዬ በበኩላቸው የምርምር እና የጥናት ተቋማት ገለልተኛ ሆነው የሀገርን ብሔራዊ ጥቅም እና የህዝብንም ተጠቃሚነት በመጠበቅ ሃሳባቸውን ነጻ ሆነው ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል ያሉ ሲሆን ምክር ቤቱም ይህንን ውጤት እንደ ግብዓት እየተጠቀመ አሰራሩን ለማሻሻል ሊጠቀምበት ይገባል ብለዋል፡፡
ብሪጅ ሪሰርች ኢኖቬሽን ከምርምርና ጥናት ስራው በተጨማሪ በምስራቅ አፍሪካ የሰላምና የልማት ስራዎች ላይ እንደሚሳተፍም ሰምተናል፡፡
የምርምርና የጥናት ተቋሙን ያቋቋሙት የረዥም ዓመት ልምድ ያላቸው በህግ፣ በፖለቲካል ሳይንስ፣ በታሪክ ላይ ጥናትና ምርምር በሚያደርጉ ምሁራን እንደሆነ ተነግሯል፡፡
ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…
ማርታ በቀለ
የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇
🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s








